News Detail

Global News
Aug 24, 2020 757 views

በካናዳ አብዛኞቹ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ማቀዳቸውን አንድ ጥናት አመላከተ።

በ ካናዳ በተካሄደ አንድ ጥናት አብዛኛው ካናዳዊያን ቤተሰብ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ማቀዳቸውን ነገር ግን በ አካባቢው የኮሮና ቫይረስ ስርጭቱ በይበልጥ ከተሰፉፉ ትምህርት እንዲቋረጥ እንደሚፈልጉ አመላክቷል።

በ ሌገር እና በካናዳ  ጥናት ማህበር የተካሄደው ጥናት  በአካባቢው ትምህርት ቤቶች ከመከፈታቸው በፊት የወላጆችን ፍላጎት ምን እንደሚመስል ለማወቅ የተካሄደ ጥናት ነው።

በጥናቱም ጥያቄው ከቀረበላቸው እና ምላሽ ከሰጡት 66%  ተሳታፊዋች ውሰጥ 63% የሚሆኑት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ማቀዳቸውን አሳውቀዋል። 

ከዚህ ውስጥም 69% የሚሆኑት የ ቫይረሱ ስርጭት የሚጨምር ከሆነ   ትምህርት እንዲቋረጥ እና የመማር ማስተማሩ ሂደት በቤት ውስጥ እንዲሆን እንደሚፈልጉም ጥናቱ አመላክቷል።

በ ኦላይን በተካሄደው  በዚህ የዳሰሳ ጥናት ከ 18 አመት በላይ የሆኑ 1,510 ተማሪዋች 385 ወላጆች ተሳትፈውበታል። 

 በተያያዘም በጥናቱ 76%  የሚሆኑ መላሾች የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ተማሪዋች ወደ ትምህርት ቤት ሲመለሱ  የአፍ መሸፈኛ ጭንብል ያድርጉ ማለታቸውንም ጥናቱ አስታውቋል ።

በካናዳ ትምህርት ቤቶች ከተከፈቱ ሁለት ሳምንት ሆኗል።

Recent News
Follow Us