በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዘርፉ ውጤታማ ለመሆን የተናበበ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥራት ያለው ትምህርት በማግኘት ረገድ እኩል እድል እንዲኖረው ፤ በድሃና ሃብታም መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ ሥራ መስራት አለብን ብለዋል።
ይችን ሀገር መለወጥ የሚቻለው የትምህርት ሥርዓቱን መቀየር ሲቻል መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሩ በርካታ ሪፎርሞች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖር ማድረግ ላይ መሥራት እንደሚገባ አንስተው በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል የተጀመረው ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ከፈተና ጋር በተያያዘ በዚህ ዓመት 150 ሺ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን ባለው ሁኔታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የተማሪ መጽሐፍት አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉን ገልፀው የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተማሪ መጽሐፍ አንድ ለአንድ ያልደረሰ በመሆኑ ክልሎች በትኩረት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የመምህራንን አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከተመረቁ ዜጎች ውስጥ ልዩ የማስተማር ሙያ (pedagogy) ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ሙያው እንዲገቡ እንደሚደረግም ገልፀዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ይህ የምክክር መድረክ በዘርፉ ባለፉት ስድስት ወራት የተፈፀሙ ዋና ዋና ተግባራት ላይ የሚመክር መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ የሪፎርምና ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ላይ አንዱ ከአንዱ ተሞክሮ የሚወስድበት ፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና መፍትዎች ላይ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫ የሚቀመጥበት እንደሆነም አብራርተዋል።
በምክክር መድረኩ የክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዘርፉ ውጤታማ ለመሆን የተናበበ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥራት ያለው ትምህርት በማግኘት ረገድ እኩል እድል እንዲኖረው ፤ በድሃና ሃብታም መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ ሥራ መስራት አለብን ብለዋል።
ይችን ሀገር መለወጥ የሚቻለው የትምህርት ሥርዓቱን መቀየር ሲቻል መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሩ በርካታ ሪፎርሞች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖር ማድረግ ላይ መሥራት እንደሚገባ አንስተው በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል የተጀመረው ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ከፈተና ጋር በተያያዘ በዚህ ዓመት 150 ሺ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን ባለው ሁኔታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የተማሪ መጽሐፍት አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉን ገልፀው የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተማሪ መጽሐፍ አንድ ለአንድ ያልደረሰ በመሆኑ ክልሎች በትኩረት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የመምህራንን አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከተመረቁ ዜጎች ውስጥ ልዩ የማስተማር ሙያ (pedagogy) ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ሙያው እንዲገቡ እንደሚደረግም ገልፀዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ይህ የምክክር መድረክ በዘርፉ ባለፉት ስድስት ወራት የተፈፀሙ ዋና ዋና ተግባራት ላይ የሚመክር መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ የሪፎርምና ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ላይ አንዱ ከአንዱ ተሞክሮ የሚወስድበት ፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና መፍትዎች ላይ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫ የሚቀመጥበት እንደሆነም አብራርተዋል።
በምክክር መድረኩ የክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።