News

National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ጋር ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሃንፊልድ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸው የትምህርት ሚኒስትሩ በትምህርት ሥርዓቱ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ በማድረግ ተወዳዳሪና ብቁ ትውልድ ለመፍጠር እየተተገበሩ ስላሉ የሪፎርም ሥራዎች እና ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አብራርተዋል።
በዚህም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትምህርት ዘርፉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን፣ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ የትምህርት ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራሳቸውን የሚያስተዳድሩ፣ ነጻ ሃሳብ የሚራመድባቸው፣ ትክክለኛ የማስተማሪያና የምርምር ተቋማት እንዲሆኑ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን እንዲደግፉም ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሃንፊልድ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ጀርመን ለረጅም ጊዜ የቆየ መልካም ግንኙነት እንደነበራቸው ገልጽው ይህንን አጠናክረው መቀጠል እንደሚፈልጉም ተናግረዋል።
በተለይም በክቡር ሚኒስትሩ የቀረቡትን በኢትዮጵያ የጀርመን ትምህርት ቤት ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች የነጻ የትምህርት እድል የሚያገኙበትን፣ በሰው ሰራሽና ተፈጥሮ አደጋ የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ በመገንባትና በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ስራዎችን በመደግፍ ረገድ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩም አብራርተዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሃንፊልድ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸው የትምህርት ሚኒስትሩ በትምህርት ሥርዓቱ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ በማድረግ ተወዳዳሪና ብቁ ትውልድ ለመፍጠር እየተተገበሩ ስላሉ የሪፎርም ሥራዎች እና ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አብራርተዋል።
በዚህም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትምህርት ዘርፉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን፣ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ የትምህርት ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራሳቸውን የሚያስተዳድሩ፣ ነጻ ሃሳብ የሚራመድባቸው፣ ትክክለኛ የማስተማሪያና የምርምር ተቋማት እንዲሆኑ ለማድረግ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን እንዲደግፉም ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ጄንስ ሃንፊልድ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ጀርመን ለረጅም ጊዜ የቆየ መልካም ግንኙነት እንደነበራቸው ገልጽው ይህንን አጠናክረው መቀጠል እንደሚፈልጉም ተናግረዋል።
በተለይም በክቡር ሚኒስትሩ የቀረቡትን በኢትዮጵያ የጀርመን ትምህርት ቤት ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች የነጻ የትምህርት እድል የሚያገኙበትን፣ በሰው ሰራሽና ተፈጥሮ አደጋ የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ በመገንባትና በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ስራዎችን በመደግፍ ረገድ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩም አብራርተዋል።
Jan 17, 2025 72
National News

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ የሚሰጠውን የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተናን ዳግም ለመውሰድ ፍላጎት ያላችሁ አመልካቾች

 ይህንን ሊንክ https://exam.ethernet.edu.et በመጫን መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

 ይህንን ሊንክ https://exam.ethernet.edu.et በመጫን መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

Jan 16, 2025 265
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባስደርን በጽ/ ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ከሆኑት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር ጋር ተወያይተዋል።
በዚሁ ወቅት ትምህርት ሚኒስቴር ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በአጠቃላይና በከፍተኛ ትምህርት ዘርፎች እየተተገበሩ ያሉ የለውጥ እርምጃዎችንና የትኩረት አቅጣጫዎችን ለአምባሰደሯ አብራርተዋል።
በተለይም ጥራት ያለው ፍትሃዊ ትምህርት ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የቅድመ ልጅነት ትምህርት፣ የመምህራንን የማስተማር አቅም ማሳደግ፣ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ ማድረግ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።
አክለውም በትምህርት ዘርፉ ድጋፍ የሚያደርጉ አጋር አካላት የቅድሚያ ትኩረት የተሰጣቸውና የተማሪዎችን እኩል የመማር መብት የሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ መሆን እንዳለበት ገልጸው ለዚህም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመወያየት በጋራ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገርን በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥቶ እየስራቸው ላሉ ስራዎች አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገላጸዋል።
ሁለቱ አካላት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው በሚቀጥሉበት ጉዳይ ላይም ሰፊ ውይይት አድረገዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ከሆኑት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገር ጋር ተወያይተዋል።
በዚሁ ወቅት ትምህርት ሚኒስቴር ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በአጠቃላይና በከፍተኛ ትምህርት ዘርፎች እየተተገበሩ ያሉ የለውጥ እርምጃዎችንና የትኩረት አቅጣጫዎችን ለአምባሰደሯ አብራርተዋል።
በተለይም ጥራት ያለው ፍትሃዊ ትምህርት ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ፣ የትምህርት ቤት ምገባ፣ የቅድመ ልጅነት ትምህርት፣ የመምህራንን የማስተማር አቅም ማሳደግ፣ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ማሻሻል እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ ማድረግ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።
አክለውም በትምህርት ዘርፉ ድጋፍ የሚያደርጉ አጋር አካላት የቅድሚያ ትኩረት የተሰጣቸውና የተማሪዎችን እኩል የመማር መብት የሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ መሆን እንዳለበት ገልጸው ለዚህም ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመወያየት በጋራ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገርን በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥቶ እየስራቸው ላሉ ስራዎች አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገላጸዋል።
ሁለቱ አካላት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው በሚቀጥሉበት ጉዳይ ላይም ሰፊ ውይይት አድረገዋል።
Jan 14, 2025 43
National News

ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ የልዩ ትምህርት ፍላጎት ያላቸው ዜጎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡና ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የሁሉንም ባለድርሻዎችና አጋሮች ድጋፍና ትብብር እንደሚፈልግ ተገለጸ።

በልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ላይ ከአካል ጉዳተኞች ማህበራት ጋር ምክክር ተደርጓል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የምክክር መድረኩን ሲከፍቱ እንደገለጹት እድሜያቸው ለትምህርት የደረሰና ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ሁሉም ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸው ህጻናት ወጣቶችና ጎልማሶች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡና ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የሁሉንም ተሳትፎ የሚጠይቅ ተግባር ነው።
ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸውን ዜጎች የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሻሻልና አካቶ ትምህርትን ለመተግበር በስራው ዙሪያ ንቁ ተሳትፎ ካላቸው የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና አጋሮች ጋር በትብብር መስራቱ ለስራው ውጤታማነት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል፡፡
በ2015 ዓ.ም በወጣው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ልዩ ተሰጥዎና ተውህቦ ያላቸው፣ የአካል ጉዳትና ልዩ የመማር ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች የሚያስተናግድ ስርአተ ትምህርት ተዘጋጅቶ ስራ ላይ እንዲውል አቅጣጫ መቀመጡንም ሚኒስትር ዴኤታዋ አመልክተዋል፡።
ልዩ ፍላጎት ያላቸው ሁሉም ህፃናት ወጣቶችና ጎልማሶች የትምህርት ጥራትና ተገቢነት ያለው ፍትሃዊ የሆነ ትምህርትና ስልጠና ተደራሽ በማድረግ በአገራቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ውስጥ ሙሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ የሚያስችል የአካቶ ትምህርት ስርዓትን ለመገንባት ስትራቴጂ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል፡፡
የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራትና መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዩሀንስ ወጋሶ በበኩላቸው ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግና በትምህርት ቤት ውስጥ የሚያገኙትን ትምህርት ለማሻሻል በተዘጋጀው የልዩ ትምህርት ስትራቴጂ የተቀመጡ ዋና ዋና ምሶሶዎችን በመተግበር የልዩ ፍላጎት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡።
የአርብቶ አደርና የልዩ ፍላጎት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ መሠረት በቀለ በዚሁ ወቅት ባቀረቡት ጽሁፍ ወደ ትምህርት ቤት ያልመጡና ትምህርት ቤቶችም ምቹ ባለመሆናቸው ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ በርካታ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ተማሪዎች መኖራቸውን ጠቁመው የድጋፍ መስጫ ማዕካትን በማቋቋምና የመምህራንን ክህሎት በማሳደግ የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡
የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው ማህበራት ህብረተሰቡን ማንቃትና በሚሰሩ ስራዎች ላይም የሚያስፈልጉ ምክረ ሀሳቦችን በመስጠት የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሳደግ በጋራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል።
በልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት ላይ ከአካል ጉዳተኞች ማህበራት ጋር ምክክር ተደርጓል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የምክክር መድረኩን ሲከፍቱ እንደገለጹት እድሜያቸው ለትምህርት የደረሰና ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ሁሉም ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸው ህጻናት ወጣቶችና ጎልማሶች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡና ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የሁሉንም ተሳትፎ የሚጠይቅ ተግባር ነው።
ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸውን ዜጎች የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሻሻልና አካቶ ትምህርትን ለመተግበር በስራው ዙሪያ ንቁ ተሳትፎ ካላቸው የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና አጋሮች ጋር በትብብር መስራቱ ለስራው ውጤታማነት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል፡፡
በ2015 ዓ.ም በወጣው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ልዩ ተሰጥዎና ተውህቦ ያላቸው፣ የአካል ጉዳትና ልዩ የመማር ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች የሚያስተናግድ ስርአተ ትምህርት ተዘጋጅቶ ስራ ላይ እንዲውል አቅጣጫ መቀመጡንም ሚኒስትር ዴኤታዋ አመልክተዋል፡።
ልዩ ፍላጎት ያላቸው ሁሉም ህፃናት ወጣቶችና ጎልማሶች የትምህርት ጥራትና ተገቢነት ያለው ፍትሃዊ የሆነ ትምህርትና ስልጠና ተደራሽ በማድረግ በአገራቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ውስጥ ሙሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ የሚያስችል የአካቶ ትምህርት ስርዓትን ለመገንባት ስትራቴጂ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል፡፡
የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራትና መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዩሀንስ ወጋሶ በበኩላቸው ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግና በትምህርት ቤት ውስጥ የሚያገኙትን ትምህርት ለማሻሻል በተዘጋጀው የልዩ ትምህርት ስትራቴጂ የተቀመጡ ዋና ዋና ምሶሶዎችን በመተግበር የልዩ ፍላጎት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡።
የአርብቶ አደርና የልዩ ፍላጎት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ መሠረት በቀለ በዚሁ ወቅት ባቀረቡት ጽሁፍ ወደ ትምህርት ቤት ያልመጡና ትምህርት ቤቶችም ምቹ ባለመሆናቸው ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ በርካታ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ተማሪዎች መኖራቸውን ጠቁመው የድጋፍ መስጫ ማዕካትን በማቋቋምና የመምህራንን ክህሎት በማሳደግ የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡
የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ ጉጆ በበኩላቸው ማህበራት ህብረተሰቡን ማንቃትና በሚሰሩ ስራዎች ላይም የሚያስፈልጉ ምክረ ሀሳቦችን በመስጠት የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተጠቃሚነት ለማሳደግ በጋራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድተዋል።
Jan 05, 2025 46
National News

በማዕከላዊ ቀጠና ስር የተመደበው የኦሮምያ ብሄራዊ ክልል የተማሪዎች የስፖርት ሊግን አስጀመረ።

በኦሮምያ ክልል የትምህርት ቤቶች የስፖርት ሊግ ውድድር በአዳማ ከተማ በስምንት የመንግስት አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች መካሄድ ጀምሯል።
ስፖርትዊ ውድድሩ የክልሉና የአዳማ ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል።
ውድድሮቹ የተጀመሩት በእግር ኳስ፣ በቮሊቦል እና በአትሌቲክስ ስፖርት አይነቶች ሲሆን በሁሉም ውድድሮች በርካታ ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የስፖርት ውድድሩ ተማሪዎች ያላቸውን መልካም ግንኙነት ከማጠናከር ባለፈ በአካልና በአእምሮ እንዲሁም ሁለንተናዊ ስብዕና የተላበሱ ቀልጣፋ ዜጋ እንዲሆኑ እንደሚያደርጋቸው በማስጀመሪያ መድረኩ ላይ ተገልጿል።
በተጨማሪም ስፖርታዊ ውድድሩ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማሳለጥ የጤናና የሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ትልቅ ሚናና ድርሻ እንዳለው በማመን ወደ ስራ የተገባ መሆኑም ተገልጿል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የተማሪዎች የስፖርት ውድድር በተለያዩ የምድብ ቀጠናዎች እየተካሄደ ይገኛል።
በኦሮምያ ክልል የትምህርት ቤቶች የስፖርት ሊግ ውድድር በአዳማ ከተማ በስምንት የመንግስት አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች መካሄድ ጀምሯል።
ስፖርትዊ ውድድሩ የክልሉና የአዳማ ከተማ አስተዳደር አመራሮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል።
ውድድሮቹ የተጀመሩት በእግር ኳስ፣ በቮሊቦል እና በአትሌቲክስ ስፖርት አይነቶች ሲሆን በሁሉም ውድድሮች በርካታ ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የስፖርት ውድድሩ ተማሪዎች ያላቸውን መልካም ግንኙነት ከማጠናከር ባለፈ በአካልና በአእምሮ እንዲሁም ሁለንተናዊ ስብዕና የተላበሱ ቀልጣፋ ዜጋ እንዲሆኑ እንደሚያደርጋቸው በማስጀመሪያ መድረኩ ላይ ተገልጿል።
በተጨማሪም ስፖርታዊ ውድድሩ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማሳለጥ የጤናና የሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ትልቅ ሚናና ድርሻ እንዳለው በማመን ወደ ስራ የተገባ መሆኑም ተገልጿል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የተማሪዎች የስፖርት ውድድር በተለያዩ የምድብ ቀጠናዎች እየተካሄደ ይገኛል።
Dec 25, 2024 118
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአገሪቱን እድገትና የህዝቡን ህይወት ለማሻሻል ቅድሚያ ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስገነዘቡ።

ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ሰባት (47) የመንግስተት ዩኒቨርስቲዎች ጋር በ2017 የሚተገበር ቁልፍ የአፈጻጸመም ውል ተፈራርሟል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በስምምነቱ ወቅተት እንደገለጹት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሯቸው ምርምሮችና የሚያፈሯቸው ዜጎች አገር የሚለውጡና ከዓለም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል።
ዩኒቨርስቲዎች ራሳቸውን ወደ ራስገዝነት እያሳደጉ እድገታቸውንና ቀጣይነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የተፈረመው ውል ሃላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የትምህርትና የምርምር ጥራትን በማስጠበቅ ብቃትና ጥራት ያለው ዜጋ ማፍራት ግዴታ መሆኑን አውቀው በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
በቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ ስምምነቱ መሠረት ውጤት የሚያስመዘግቡ ተቋማት በበጀት ጭምር የበለጠ የሚደገፉበት፣ ወደ ኋላ የሚቀሩና ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት እንደሆነ ጠቁመዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የቁልፍ ስራዎች አፈጻጸም ውሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያዎች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እንደሚያስችል ገልጸዋል።
ስምምነቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ስርዓት እንዲኖርና ዩኒቨርስቲዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ጠቅሰዋል።
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርተ ተቋማቱ በገቡት ስምምነት መሠረት ስራዎቻቸውን በየደረጃው በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ለማስመዝገብ መረባረብ እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትሩን በመወከል የከፍተኛ ትምህርቶ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አት ኮራ ጡሹኔ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል ደግሞ የየዩኒቨርስቲዎቹ ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች ፈርመዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ሰባት (47) የመንግስተት ዩኒቨርስቲዎች ጋር በ2017 የሚተገበር ቁልፍ የአፈጻጸመም ውል ተፈራርሟል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በስምምነቱ ወቅተት እንደገለጹት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሯቸው ምርምሮችና የሚያፈሯቸው ዜጎች አገር የሚለውጡና ከዓለም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል።
ዩኒቨርስቲዎች ራሳቸውን ወደ ራስገዝነት እያሳደጉ እድገታቸውንና ቀጣይነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የተፈረመው ውል ሃላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የትምህርትና የምርምር ጥራትን በማስጠበቅ ብቃትና ጥራት ያለው ዜጋ ማፍራት ግዴታ መሆኑን አውቀው በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
በቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ ስምምነቱ መሠረት ውጤት የሚያስመዘግቡ ተቋማት በበጀት ጭምር የበለጠ የሚደገፉበት፣ ወደ ኋላ የሚቀሩና ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት እንደሆነ ጠቁመዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የቁልፍ ስራዎች አፈጻጸም ውሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያዎች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እንደሚያስችል ገልጸዋል።
ስምምነቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ስርዓት እንዲኖርና ዩኒቨርስቲዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ጠቅሰዋል።
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርተ ተቋማቱ በገቡት ስምምነት መሠረት ስራዎቻቸውን በየደረጃው በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ለማስመዝገብ መረባረብ እንዳለባቸው ተናግረዋል።
ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትሩን በመወከል የከፍተኛ ትምህርቶ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አት ኮራ ጡሹኔ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል ደግሞ የየዩኒቨርስቲዎቹ ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች ፈርመዋል።
Dec 25, 2024 198
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ስራ በውጤታማነት ለመፈጸም የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።

በትምህርት ሚኒስቴርና በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል ነገ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም የሚፈረመው ስምምነት ተቋማት ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን በማፍራት ሂደት ውስጥ ተጠያቂነትን ከማስፈን ባለፈ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒሰትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች / Key Performance Indicators / 47 ዩኒቨርስቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ድርድር ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት ከተያዘው 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ዩኒቨርስቲዎች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪና ለስራ ገበያው የሚመጥን ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን ማፍራት እንዲችሉ ከተያዘው 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ስራን በውጤት መምራት ወደሚያስችል ስርዓት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ተቋማቱ ስራን በውጤት መምራት ወደሚያችል ስርዓት ማስገባት በሙያዊና ክህሎታዊ ስራዎች እንዲሁም በልህቀት ላይ በማተኮር የአገሪቱን ችግሮች መፍታት የሚችሉ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚን የማልማት ስራ ላይ የበኩላቸውን ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱ እንደሚያስችላቸው ክቡር አቶ ኮራ ገልጸዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፈነ አመራር እንዲከተሉ ፣ አገሪቱ ለምታወጣው ሀብት ተመጣጣኝ ውጤት እንዲያስገኙ የአፈጻጸም አቅማቸው እንዲገመገምና ለስኬቱም እውቅና እና ሽልማት እንዲያገኙ እንደሚያግዝም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡
የጅጅጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር በሽር አብዱላሂ በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ ስምምነቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስራዎችን ከስር ከመሰረታቸው በአግባቡ በመያዝ ከሚፈለገው ግብ ላይ ለመድረስና የተጠያቂነትና ውጤታማ የሀብት አጠቃቀም ስርዓት እንዲኖር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ብርሃነ መስቀል ጠና በበኩላቸው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ በትምህርት ባለሙያዎችና በመምህራን ትምህርት ላይ አተኩሮ የሚሰራ ተቋም እንደመሆኑ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ድርድርና ስምምነት የተደረገባቸው ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች ስራን ቆጥሮ በመረከብ በውጤታማነት ለመፈጸም እንደሚያችል ተናግረዋል፡፡
የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጴጥሮስ ወ/ ጊዮርጊስ ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች ዩኒቨርስቲዎች ወዴት እንደሚሄዱና የት ቦታ ለመድረስ ማቀድ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ውል መሆኑን ጠቁመው ከትምህርት ተቋማት ውጪ የሚገኙ ሌሎች ተቋማትም ቢተገብሩት ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው አስረድተዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ስራን በውጤት መምራት ወደሚያችል ስርዓት ለማስገባት ሚያስችለው / KPI / ስምምነት 47ቱም የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶችና የቦርድ ሰብሳቢዎች ከትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር በነገው እለት በሚኖር ስነ ስርዓት በይፋ ይፈራረማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴርና በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል ነገ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም የሚፈረመው ስምምነት ተቋማት ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን በማፍራት ሂደት ውስጥ ተጠያቂነትን ከማስፈን ባለፈ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒሰትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች / Key Performance Indicators / 47 ዩኒቨርስቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ድርድር ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት ከተያዘው 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ዩኒቨርስቲዎች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪና ለስራ ገበያው የሚመጥን ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን ማፍራት እንዲችሉ ከተያዘው 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ስራን በውጤት መምራት ወደሚያስችል ስርዓት ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ተቋማቱ ስራን በውጤት መምራት ወደሚያችል ስርዓት ማስገባት በሙያዊና ክህሎታዊ ስራዎች እንዲሁም በልህቀት ላይ በማተኮር የአገሪቱን ችግሮች መፍታት የሚችሉ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በማድረግ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚን የማልማት ስራ ላይ የበኩላቸውን ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱ እንደሚያስችላቸው ክቡር አቶ ኮራ ገልጸዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፈነ አመራር እንዲከተሉ ፣ አገሪቱ ለምታወጣው ሀብት ተመጣጣኝ ውጤት እንዲያስገኙ የአፈጻጸም አቅማቸው እንዲገመገምና ለስኬቱም እውቅና እና ሽልማት እንዲያገኙ እንደሚያግዝም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡
የጅጅጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር በሽር አብዱላሂ በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ ስምምነቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስራዎችን ከስር ከመሰረታቸው በአግባቡ በመያዝ ከሚፈለገው ግብ ላይ ለመድረስና የተጠያቂነትና ውጤታማ የሀብት አጠቃቀም ስርዓት እንዲኖር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ብርሃነ መስቀል ጠና በበኩላቸው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ በትምህርት ባለሙያዎችና በመምህራን ትምህርት ላይ አተኩሮ የሚሰራ ተቋም እንደመሆኑ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ድርድርና ስምምነት የተደረገባቸው ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች ስራን ቆጥሮ በመረከብ በውጤታማነት ለመፈጸም እንደሚያችል ተናግረዋል፡፡
የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጴጥሮስ ወ/ ጊዮርጊስ ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች ዩኒቨርስቲዎች ወዴት እንደሚሄዱና የት ቦታ ለመድረስ ማቀድ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ውል መሆኑን ጠቁመው ከትምህርት ተቋማት ውጪ የሚገኙ ሌሎች ተቋማትም ቢተገብሩት ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው አስረድተዋል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ስራን በውጤት መምራት ወደሚያችል ስርዓት ለማስገባት ሚያስችለው / KPI / ስምምነት 47ቱም የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶችና የቦርድ ሰብሳቢዎች ከትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር በነገው እለት በሚኖር ስነ ስርዓት በይፋ ይፈራረማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
Dec 24, 2024 148
National News

የት/ቤቶች ስፖርት ውድድር ለሀገራዊ ስፖርት ውጤታማነት የላቀ ሚና እንዳለው ተጠቆመ።

የ2017 የት/ቤቶች የስፖርት ውድድር ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ ወቅት በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት መሰረተ ልማትና አገልግሎት ዴስክ ሃላፊ አቶ ታየ ግርማ እንደገለጹት የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድርን ማጠናከር ሳይቻል ሀገራዊ የስፖርት ውጤት መጠበቅ አይቻልም።
በተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የነበረው የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር በያዝነው የትምህርት ዘመን በዘጠኝ ቀጠናዎች ተደራጅቶ እየተከናወነ መሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል።
በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የውድድር ስፖርቶች ክትትልና ድጋፍ ዴስክ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ዳርጌ የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር የተፈጠረውን ሀገራዊ የስፖርታዊ ውጤቶች መቀዛቀዝ ክፍተት ለመሙላት ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስቴሩ ለት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድሮች ትኩረት በመስጠት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ስራ የተገባ መሆኑን ጠቁመው ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር በት/ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ቦጋለ በበኩላቸው ስፖርቱ በማህበረሰቡ ድጋፍ እንዲያገኝ ሁላችንም በአገኘነው አጋጣሚ ሁሉ የማስተዋወቅ ስራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።
በዘጠኙም ቀጠናዎች የተደለደሉ ሁሉም ክልሎች የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን ከጥቂት ቀጠናዎች በስተቀር የስፖርት ሊጉን ስኬታማ ለማድረግ የአመራር ሚና በሚፈለገው ልክ ባለመሆኑ ይህ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቁሟል።
የ2017 የት/ቤቶች የስፖርት ውድድር ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ ወቅት በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት መሰረተ ልማትና አገልግሎት ዴስክ ሃላፊ አቶ ታየ ግርማ እንደገለጹት የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድርን ማጠናከር ሳይቻል ሀገራዊ የስፖርት ውጤት መጠበቅ አይቻልም።
በተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የነበረው የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር በያዝነው የትምህርት ዘመን በዘጠኝ ቀጠናዎች ተደራጅቶ እየተከናወነ መሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል።
በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የውድድር ስፖርቶች ክትትልና ድጋፍ ዴስክ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ዳርጌ የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድር የተፈጠረውን ሀገራዊ የስፖርታዊ ውጤቶች መቀዛቀዝ ክፍተት ለመሙላት ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስቴሩ ለት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድሮች ትኩረት በመስጠት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ስራ የተገባ መሆኑን ጠቁመው ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር በት/ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ቦጋለ በበኩላቸው ስፖርቱ በማህበረሰቡ ድጋፍ እንዲያገኝ ሁላችንም በአገኘነው አጋጣሚ ሁሉ የማስተዋወቅ ስራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።
በዘጠኙም ቀጠናዎች የተደለደሉ ሁሉም ክልሎች የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን ከጥቂት ቀጠናዎች በስተቀር የስፖርት ሊጉን ስኬታማ ለማድረግ የአመራር ሚና በሚፈለገው ልክ ባለመሆኑ ይህ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቁሟል።
Dec 23, 2024 111
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕፌሰር ብርሃኑ ነጋ በደቡብ ሱዳን መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ገብሬላ ቻንግሰን ቻንግ የተመራ ልዑክን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ዜጎች እየሰጠች ባለችው የትምህርት እድልና ባጋጠሙ ችግሮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን ዜጎች ባለፉት አመታት በርካታ የትምህርት እድል ሲሰጥ መቆየቱን አንስተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ተወዳዳሪ፣ ብቁ እና ክህሎት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት እየሰራቸው ያሉ ሪፎርሞችን ለሉካን ቡድኑ ያብራሩ ሲሆን የነጻ የትምህርት እድል የተሰጣቸው ተማሪዎችም ሲመረጡ ይህንን ታሳቢ ያደርጉ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በተለይም የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተናን እንዲሁም የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተናን እንደሚወስዱ አውቀው ሲመረጡ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ጠንካራ መግቢያ ፈተና መስጠት እንዳለባቸውና ተማሪዎች ትምህርታቸውን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባቸውም አብራርተዋል።
የደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ክቡር ገብሬላ ቻንግሰን በበኩላቸው ከሁለት ዓመት በፊት የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት በጥሩ ሁኔታ እየተፈጸመ መሆኑን ገልጸው የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን ዜጎች በተሰጠው የነጻ ትምህርት እድልና እየተደረገላቸው ባለው ድጋፍ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብን አመስግነዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ ጥራትና ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት እየሰራች ያለውን ሥራ አድንቀው በደቡብ ሱዳንም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ጠንካራ እንዲሆን በማድረግ በኢትዮጵያ የትምህርት እድል የሚሰጣቸው ተማሪዎችም የተሻለ ውጤትና ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ እንሰራለን ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት ባደረጉት ውይይትም የትምህርት እድል የተሰጣቸው ተማሪዎች ከቪዛ፣ ከመኖሪያ፣ ከትራንስፖርት እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲ ቆይታ ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳይ ላይ ከተወያዩ በኋላ የየድርሻቸውን ለመወጣት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ገብሬላ ቻንግሰን ቻንግ የተመራ ልዑክን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ዜጎች እየሰጠች ባለችው የትምህርት እድልና ባጋጠሙ ችግሮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን ዜጎች ባለፉት አመታት በርካታ የትምህርት እድል ሲሰጥ መቆየቱን አንስተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ተወዳዳሪ፣ ብቁ እና ክህሎት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት እየሰራቸው ያሉ ሪፎርሞችን ለሉካን ቡድኑ ያብራሩ ሲሆን የነጻ የትምህርት እድል የተሰጣቸው ተማሪዎችም ሲመረጡ ይህንን ታሳቢ ያደርጉ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በተለይም የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተናን እንዲሁም የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተናን እንደሚወስዱ አውቀው ሲመረጡ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ጠንካራ መግቢያ ፈተና መስጠት እንዳለባቸውና ተማሪዎች ትምህርታቸውን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባቸውም አብራርተዋል።
የደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ትምህርት ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ክቡር ገብሬላ ቻንግሰን በበኩላቸው ከሁለት ዓመት በፊት የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት በጥሩ ሁኔታ እየተፈጸመ መሆኑን ገልጸው የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን ዜጎች በተሰጠው የነጻ ትምህርት እድልና እየተደረገላቸው ባለው ድጋፍ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብን አመስግነዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ ጥራትና ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች ለማፍራት እየሰራች ያለውን ሥራ አድንቀው በደቡብ ሱዳንም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ጠንካራ እንዲሆን በማድረግ በኢትዮጵያ የትምህርት እድል የሚሰጣቸው ተማሪዎችም የተሻለ ውጤትና ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ እንሰራለን ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት ባደረጉት ውይይትም የትምህርት እድል የተሰጣቸው ተማሪዎች ከቪዛ፣ ከመኖሪያ፣ ከትራንስፖርት እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲ ቆይታ ጋር በተያያዘ ያሉ ችግሮችን መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳይ ላይ ከተወያዩ በኋላ የየድርሻቸውን ለመወጣት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
Dec 16, 2024 248
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የጀኔራል ዋቁ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎበኙ።

ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የሚገኘውን ጀኔራል ዋቁ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸው ወቅትም ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርት የሚፈልገው ጥረት መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ተማሪዎች ጠንክረው መማርና ማጥናት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በትምህርት ሥርዓቱ የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን ማስተካከል ያስፈለገው የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ሀገር የሚረከቡ እውነተኛ ዜጎችን ለማፍራት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል።
ኩረጃ ለጊዜው የሚጠቅም ሊመስል ይችላል ነገር ግን ሄዶ ሄዶ ራስንም ሀገርንም ይጎዳል ያሉት ሚኒስትሩ ኩረጃን የሚጸየፉ በራሳቸው የሚሰሩና የሚተማመኑ ተማሪዎች መሆን እንዳለበቸውም አሳስበዋል።
የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ትውልዱ ይህችን ሀገር የመገንባት የወደፊት ሀላፊነቱን በታማኝነት እንዲወጣ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት በትምህርት ሴክተሩ እየተከናወኑ መሆኑንም አብራርዋል ።
አክለውም ነገ ብቁ ሀገር ተረካቢ ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ተማሪዎች ትምህርታቸው ላይ ብቻ አተኩረው እንዲማሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የሚገኘውን ጀኔራል ዋቁ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸው ወቅትም ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርት የሚፈልገው ጥረት መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ተማሪዎች ጠንክረው መማርና ማጥናት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በትምህርት ሥርዓቱ የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን ማስተካከል ያስፈለገው የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ሀገር የሚረከቡ እውነተኛ ዜጎችን ለማፍራት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል።
ኩረጃ ለጊዜው የሚጠቅም ሊመስል ይችላል ነገር ግን ሄዶ ሄዶ ራስንም ሀገርንም ይጎዳል ያሉት ሚኒስትሩ ኩረጃን የሚጸየፉ በራሳቸው የሚሰሩና የሚተማመኑ ተማሪዎች መሆን እንዳለበቸውም አሳስበዋል።
የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ትውልዱ ይህችን ሀገር የመገንባት የወደፊት ሀላፊነቱን በታማኝነት እንዲወጣ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት በትምህርት ሴክተሩ እየተከናወኑ መሆኑንም አብራርዋል ።
አክለውም ነገ ብቁ ሀገር ተረካቢ ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ተማሪዎች ትምህርታቸው ላይ ብቻ አተኩረው እንዲማሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
Dec 13, 2024 200
National News

ከኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ ስኬታማ ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲኖር እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።

የፈረንሳይ ዓለም አቀፍ የትምህርት ትብብር የሉዑካን ቡድን በትምህርት ሚኒስቴር ጉብኝት አድርጓል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ተወካይና የአስተደደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) የልዑካን ቡድኑ ከከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት እንደገለጹት ከኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲኖር እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር እንዲችሉ በወጣው የህግ ማዕቀፍ መሰረትም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆኖ በደንብ እንዲደራጅ በህግ መደንገጉንም ዶክተር ሰለሞን ተናግረዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝነት ለማጠናከር የትምህርት ሚኒስቴር ከፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ከፈረንሳይ ዩኒቨርስቲዎች ጋር የጀመረው የቴክኒክ ድጋፍና የልምድ ልውውጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ከዓለም አቀፍ ደረጃና የገበያ ፍላጎት ጋር የሚጣጣም ስርዓተ ትምህርት እንዲኖራቸው ለማስቻል እና ወጥነት ያለው የትምህርት ደረጃን ለማረጋገጥ የከፍተኛ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ማዘጋጀቱንም ተናግረዋል፡፡
በፈረንሳይ ዩኒቨርስቲዎችና በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል በትምህርት ጥራት ፣ በቴክኒክ ልምድና አቅም ግንባታና በሌሎችም ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ትብብር እንዲሁም ጠንካራ ትስስር እንዲኖር እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የፈረንሳይ ዓለም አቀፍ የትምሀርት ትብብር የልዑካን ቡድን አባላት በበኩላቸው የፈረንሳይ ዓለም አቀፍ የትምህርት ትብብር ከአፍሪካ ትምህርት ተቋማት ጋር በአቅም ግንባታ ፣በልምድ ልውውጥ፣ በተማሪዎችና መምህራን እንቅስቃሴ እና በሌሎችም ዓለም አቀፍ በሆኑ የትምህርት ልማት ስራዎች በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
የፈረንሳይ ዩኒቨርስቲዎችና ትምሀርት ተቋማት በቴክኒክ ፣ በአቅም ግንባታ ፣ በቴክኖሎጂ፣ እና በትምህርት ጥራት ማሻሻያ። ስራዎችና በሌሎችም ያላቸውን እውቀት፣ ምርጥ ተሞክሮዎችንና ልምዶችን ለማጋራትና ለማካፈል ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡
የፈረንሳይ ዓለም አቀፍ የትምህርት ትብብር የሉዑካን ቡድን በትምህርት ሚኒስቴር ጉብኝት አድርጓል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ተወካይና የአስተደደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) የልዑካን ቡድኑ ከከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት እንደገለጹት ከኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲኖር እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር እንዲችሉ በወጣው የህግ ማዕቀፍ መሰረትም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆኖ በደንብ እንዲደራጅ በህግ መደንገጉንም ዶክተር ሰለሞን ተናግረዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝነት ለማጠናከር የትምህርት ሚኒስቴር ከፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ከፈረንሳይ ዩኒቨርስቲዎች ጋር የጀመረው የቴክኒክ ድጋፍና የልምድ ልውውጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ከዓለም አቀፍ ደረጃና የገበያ ፍላጎት ጋር የሚጣጣም ስርዓተ ትምህርት እንዲኖራቸው ለማስቻል እና ወጥነት ያለው የትምህርት ደረጃን ለማረጋገጥ የከፍተኛ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ማዘጋጀቱንም ተናግረዋል፡፡
በፈረንሳይ ዩኒቨርስቲዎችና በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል በትምህርት ጥራት ፣ በቴክኒክ ልምድና አቅም ግንባታና በሌሎችም ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ትብብር እንዲሁም ጠንካራ ትስስር እንዲኖር እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
የፈረንሳይ ዓለም አቀፍ የትምሀርት ትብብር የልዑካን ቡድን አባላት በበኩላቸው የፈረንሳይ ዓለም አቀፍ የትምህርት ትብብር ከአፍሪካ ትምህርት ተቋማት ጋር በአቅም ግንባታ ፣በልምድ ልውውጥ፣ በተማሪዎችና መምህራን እንቅስቃሴ እና በሌሎችም ዓለም አቀፍ በሆኑ የትምህርት ልማት ስራዎች በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
የፈረንሳይ ዩኒቨርስቲዎችና ትምሀርት ተቋማት በቴክኒክ ፣ በአቅም ግንባታ ፣ በቴክኖሎጂ፣ እና በትምህርት ጥራት ማሻሻያ። ስራዎችና በሌሎችም ያላቸውን እውቀት፣ ምርጥ ተሞክሮዎችንና ልምዶችን ለማጋራትና ለማካፈል ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡
Dec 10, 2024 181
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ የጤና ስጋት ወደማይሆንበት ደረጃ ማድረስ እንደሚገባቸው ተጠቆመ፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ምህረተ ክርስቶስ ታምሩ በኤች አይ ቪ እና በስነ ተዋልዶ ጤና ዙሪያ በተዘጋጀ አውደጥናት ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት እየቀነሰ ቢመጣም አሁንም በቫይረሱ አዲስ የሚያዙና ለሞት የሚዳረጉ ሰዎች አሉ፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንና ተማሪዎችም የኤች አይ ቪና ስነተዋልዶ ጤና ችግሮች ተጋላጭ በመሆናቸው ከቫይረሱ ነጻ የሆነ ትውልድ እንዲፈጠር በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አመልክተዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንድም ሰው በኤች አይ ቪ ቫይረስ እንዳይያዝ ሳይዘናጉ መስራትና በሽታውን ለመከላከል የተጀመረውን ጥረት አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ወ/ሮ ምህረተክርስቶስ ተናግረዋል፡፡
በጤና ሚኒስቴር የስነ ተዋልዶ ፣ ቤተሰብ እቅድ አፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና ዴስክ ተወካዮ አቶ ሞቱማ በቀለ በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኤች አይ ቪ ብቻ ሳይሆን የስነ ተዋልዶ ጤና ሙሉ ግንዛቤ ሊኖራቸው ይገባል ብለዋል፡፡
የጤና ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በኤች አይ ቪ እና በስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ዙሪያ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ዩኒቨርስቲዎች በስነ ተዋልዶ ችግሮችን በሚመለከት ቢያንስ የ20 እና የ30 ደቂቃ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን አመቻችተው ትምህርት ሊሰጡ ይገባል ብለዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙ አጋር ተቋማት በበኩላቸው የኤች አይቪ እና ስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ሁሉንም የሚያጠቁ የጤና ስጋቶች በመሆናቸው በቅንጅትና በጋራ መቋቋምና መከላከል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም የትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ስልጠና በሚገባ ላጠናቀቁ ከዩኒቨርስቲዎች ለተወከሉ ባለድርሻዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ምህረተ ክርስቶስ ታምሩ በኤች አይ ቪ እና በስነ ተዋልዶ ጤና ዙሪያ በተዘጋጀ አውደጥናት ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የኤች አይ ቪ ቫይረስ ስርጭት እየቀነሰ ቢመጣም አሁንም በቫይረሱ አዲስ የሚያዙና ለሞት የሚዳረጉ ሰዎች አሉ፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንና ተማሪዎችም የኤች አይ ቪና ስነተዋልዶ ጤና ችግሮች ተጋላጭ በመሆናቸው ከቫይረሱ ነጻ የሆነ ትውልድ እንዲፈጠር በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አመልክተዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንድም ሰው በኤች አይ ቪ ቫይረስ እንዳይያዝ ሳይዘናጉ መስራትና በሽታውን ለመከላከል የተጀመረውን ጥረት አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ወ/ሮ ምህረተክርስቶስ ተናግረዋል፡፡
በጤና ሚኒስቴር የስነ ተዋልዶ ፣ ቤተሰብ እቅድ አፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና ዴስክ ተወካዮ አቶ ሞቱማ በቀለ በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኤች አይ ቪ ብቻ ሳይሆን የስነ ተዋልዶ ጤና ሙሉ ግንዛቤ ሊኖራቸው ይገባል ብለዋል፡፡
የጤና ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በኤች አይ ቪ እና በስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ዙሪያ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ዩኒቨርስቲዎች በስነ ተዋልዶ ችግሮችን በሚመለከት ቢያንስ የ20 እና የ30 ደቂቃ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን አመቻችተው ትምህርት ሊሰጡ ይገባል ብለዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙ አጋር ተቋማት በበኩላቸው የኤች አይቪ እና ስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ሁሉንም የሚያጠቁ የጤና ስጋቶች በመሆናቸው በቅንጅትና በጋራ መቋቋምና መከላከል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም የትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን ስልጠና በሚገባ ላጠናቀቁ ከዩኒቨርስቲዎች ለተወከሉ ባለድርሻዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡
Dec 09, 2024 171
National News

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን ተወሰነ።

ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን የምግብ ሜኑ ተቀራራቢ እንዲሆን እየሰሩ ነው።
ወቅታዊውን የምግብ ዋጋ መጨመር መነሻ በማድረግ ትምህርት ሚኒስቴር ጥናት ያደረገ ሲሆን በጥናቱ ውጤት መነሻነትም የከፍትኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ በጀት በቀን ወደ 100 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል። በተደረገው የበጀት ማሻሻያ መሰረት በተቋማቱ የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን በባለሙያዎች ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ ወቅታዊ የምግብ ዋጋ ንረትን ግምት ውስጥ በማስገባት የምግብ በጀት ማሰተካከያ መደረጉን ገልጸዋል።
ዶ/ር ሰለሞን አክለውም በሀገራችን ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ያለው የምግብ ሜኑ ተቀራራቢ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በአዲሱ የበጀት ተመን መሰረት ለዩኒቨርስቲዎቹ ባላቸው ተማሪ ቁጥር ልክ ገንዘቡ እንደሚለቀቅላቸው ጠቁመዋል።
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን የምግብ ሜኑ ተቀራራቢ እንዲሆን እየሰሩ ነው።
ወቅታዊውን የምግብ ዋጋ መጨመር መነሻ በማድረግ ትምህርት ሚኒስቴር ጥናት ያደረገ ሲሆን በጥናቱ ውጤት መነሻነትም የከፍትኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ በጀት በቀን ወደ 100 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል። በተደረገው የበጀት ማሻሻያ መሰረት በተቋማቱ የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን በባለሙያዎች ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ ወቅታዊ የምግብ ዋጋ ንረትን ግምት ውስጥ በማስገባት የምግብ በጀት ማሰተካከያ መደረጉን ገልጸዋል።
ዶ/ር ሰለሞን አክለውም በሀገራችን ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ያለው የምግብ ሜኑ ተቀራራቢ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በአዲሱ የበጀት ተመን መሰረት ለዩኒቨርስቲዎቹ ባላቸው ተማሪ ቁጥር ልክ ገንዘቡ እንደሚለቀቅላቸው ጠቁመዋል።
Dec 09, 2024 227
National News

የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎትን ለማሳደግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ።

በትምህርት ሥርዓቱ የሚስተዋለውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር ለመቅረፍ በሚቻልበ ጉዳይ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ላይ የሚስተዋለውን ችግር መቅረፍ ካልተቻለ የሚፈለገውን የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና አለም አቀፍ ተወዳደሪ የሆኑ ተማሪዎችን ማፍራት እንደማይቻል ጠቅሰው ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩርት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በተለይም ተማሪዎች የሚማሩትን ትምህርት በአግባቡ እንዲረዱና ውጤታማ እንዲሆኑ እንግሊዝኛ ቋንቋን የማንበብ፣ የመጻፍ፣ የመናገርና የማዳመጥ ክህሎታቸውን በሚገባ ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
የቀጣዩ ትውልድ እጣ ፈንታ የሚወሰነው አሁን በሚሰራው ሥራ መሆኑን በመገንዘብ የመማር ማስተማር ሥነ - ዘዴውን ማስተካከል እንዲሁም ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበትን ምቹ ሁኔታ በትምህርት ቤቶች መፍጠር ይገባልም ብለዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው የእንግሊዝኛ ቋንቋ በትምህርት ዓይነትና በማስተማሪያ ቋንቋነት በትምህርት ሥርዓቱ እየተሰጠ እንደሚገኝ ጠቅሰው ነገር ግን ከፍተኛ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር መኖሩን የሚያመላክቱ ጥናቶችን አቅርበዋል።
በዚህም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር በተማሪዎችና በመምህራን ዘንድ እንደሚስተዋል አንስተው ይህንን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል ትምህርት ቤትን መሰረት ያደረገ ሥልት ቀይሶ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ትምህርት ሚኒስቴርም https://learn-english.moe.gov.et የተሰኘ ያለ ምንም የኢንተርኔት ክፍያ የሚሰራ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፓርታል አልምቶ ወደ ሥራ ማስገባቱን የጠቀሱት መሪ ሥራ አስፈጻሚው ይህንን ፖርታል ተማሪዎች፣ መምህራን እንዲሁም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎታቸውን ማሳደግ የሚፈልጉ ዜጎች እንዲጠቀሙበት በሚገባ በማስተዋወቅ ረገድ ሚድያዎችን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመድረኩም የተለያዩ ጽሁፎች ቀረበው በተሳታፊዎች ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ተሳታፊዎችም ተማሪዎች በክፍል ውስጥና ከክፍል ውጪ ቋንቋውን እንዲጠቀሙበት እና ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያበረታታ ሁኔታ አለማኖሩ ችግሩን የጎላ እንዳደረገው ገልጸው ይህንን ለመፍታት መምህራንና ተማሪዎች በድፍረት ቋንቋውን እንዲጠቅሙና ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያደርጉ ስልቶችን መቀየስ እንደሚገባም ተናግረዋል።
በመጨረሻም የቋንቋ ክህሎትን በማሳደግ ረገድ የተሰሩ ሥራዎችና ሥልቶችን መሰረት በማድረግ ተሞክሮዎች መቀመርና ማስፋት በተለይም ክልል ከክልል፣ ትምህርት ቤት ከትምህርት ቤት ልምድ የሚለዋውጡበት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም ተመላክቷል።
በምክክር መድርኩ ከሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በትምህርት ሥርዓቱ የሚስተዋለውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር ለመቅረፍ በሚቻልበ ጉዳይ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ላይ የሚስተዋለውን ችግር መቅረፍ ካልተቻለ የሚፈለገውን የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና አለም አቀፍ ተወዳደሪ የሆኑ ተማሪዎችን ማፍራት እንደማይቻል ጠቅሰው ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩርት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በተለይም ተማሪዎች የሚማሩትን ትምህርት በአግባቡ እንዲረዱና ውጤታማ እንዲሆኑ እንግሊዝኛ ቋንቋን የማንበብ፣ የመጻፍ፣ የመናገርና የማዳመጥ ክህሎታቸውን በሚገባ ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
የቀጣዩ ትውልድ እጣ ፈንታ የሚወሰነው አሁን በሚሰራው ሥራ መሆኑን በመገንዘብ የመማር ማስተማር ሥነ - ዘዴውን ማስተካከል እንዲሁም ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበትን ምቹ ሁኔታ በትምህርት ቤቶች መፍጠር ይገባልም ብለዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው የእንግሊዝኛ ቋንቋ በትምህርት ዓይነትና በማስተማሪያ ቋንቋነት በትምህርት ሥርዓቱ እየተሰጠ እንደሚገኝ ጠቅሰው ነገር ግን ከፍተኛ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር መኖሩን የሚያመላክቱ ጥናቶችን አቅርበዋል።
በዚህም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር በተማሪዎችና በመምህራን ዘንድ እንደሚስተዋል አንስተው ይህንን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል ትምህርት ቤትን መሰረት ያደረገ ሥልት ቀይሶ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ትምህርት ሚኒስቴርም https://learn-english.moe.gov.et የተሰኘ ያለ ምንም የኢንተርኔት ክፍያ የሚሰራ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፓርታል አልምቶ ወደ ሥራ ማስገባቱን የጠቀሱት መሪ ሥራ አስፈጻሚው ይህንን ፖርታል ተማሪዎች፣ መምህራን እንዲሁም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎታቸውን ማሳደግ የሚፈልጉ ዜጎች እንዲጠቀሙበት በሚገባ በማስተዋወቅ ረገድ ሚድያዎችን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመድረኩም የተለያዩ ጽሁፎች ቀረበው በተሳታፊዎች ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ተሳታፊዎችም ተማሪዎች በክፍል ውስጥና ከክፍል ውጪ ቋንቋውን እንዲጠቀሙበት እና ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያበረታታ ሁኔታ አለማኖሩ ችግሩን የጎላ እንዳደረገው ገልጸው ይህንን ለመፍታት መምህራንና ተማሪዎች በድፍረት ቋንቋውን እንዲጠቅሙና ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያደርጉ ስልቶችን መቀየስ እንደሚገባም ተናግረዋል።
በመጨረሻም የቋንቋ ክህሎትን በማሳደግ ረገድ የተሰሩ ሥራዎችና ሥልቶችን መሰረት በማድረግ ተሞክሮዎች መቀመርና ማስፋት በተለይም ክልል ከክልል፣ ትምህርት ቤት ከትምህርት ቤት ልምድ የሚለዋውጡበት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም ተመላክቷል።
በምክክር መድርኩ ከሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
Dec 07, 2024 290
Recent News
Follow Us