News

National News

መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ 5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደርስ (5 million Ethiopian Coders) የተሰኘ ስልጠና አመቻችቷል።

መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ “5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ” የተሰኘ አዲስ የስልጠና እድል አመቻችቷል። ይህ ኢኒሼቲቭ ከአይሲቲ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ኮርሶች ጥራቱና በጥልቅ ይዘቶች በሚታወቀው በኦዳሲቲ ፕላትፎርም (Udacity Platform) የፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስና ሌሎችም ከአይሲቲ ጋር የተገናኙ ኮርሶችን ከክፍያ ነፃ ማግኘት የሚያስችል ነው።
ተማሪዎች እና መምህራን ያለምንም ወጪ በእነዚህ ኮርሶች በመመዝገብ ይህንን ልዩ የስልጠና እድል መጠቀም የሚችሉ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ውስጥ በመሳተፍና ችሎታቸውን በማጎልበት በአለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ ተወዳዳሪ መሆን ይችላሉ።
በዚህ ስልጠና ተመዝግበውና የትምህርት ይዘቶቹን ተምረው ያጠናቀቁ ተሳታፊዎች በአለም አቀፍ ድርጅቶች እውቅና ያለው እና የስራ እድልን በእጅጉ ሊያሳድግ ከሚችለው Udacity የምስክር ወረቀት ያገኛሉ።
ትምህርት ሚኒስቴር በስልጠናው እንዴት መመዝገብና መሳተፍ እንደሚቻል የሚያሳዩ መመሪያዎችን በጽሁፍና በቪዲዮ አዘጋጅቷል። ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎችና መምህራን ይሄንን በበዙ ክፍያ ይሰጥ የነበረን ስልጠና መመሪያውን ተከትሎ ብቻ በመመዝገብ በነጻ መሰልጠን ትችላላችሁ።
የመመሪያውን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/-zSmhhD5qE4 ላይ በመግባት መመልከት የምትችሉ ሲሆን በምስል የተደገፈውን መመሪያም ከዚህ ፖስት ጋር አጋርተናል።
ይሄንን ጠቃሚና ነጻ የስልጠና እድል ፍላጎቱ ላላቸውና የትምህርት ዝግጅታቸው ከዚህ ስልጠና ጋር ለሚገናኝ ጓደኞቻችሁ፣ ወዳጅ ፣ ቤተሰባችሁ እንዲሁም ተማሪዎችና መምህራን በማጋራት ተጨቃሚ እንዲሆኑ አድርጉ።
መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ “5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ” የተሰኘ አዲስ የስልጠና እድል አመቻችቷል። ይህ ኢኒሼቲቭ ከአይሲቲ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ኮርሶች ጥራቱና በጥልቅ ይዘቶች በሚታወቀው በኦዳሲቲ ፕላትፎርም (Udacity Platform) የፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስና ሌሎችም ከአይሲቲ ጋር የተገናኙ ኮርሶችን ከክፍያ ነፃ ማግኘት የሚያስችል ነው።
ተማሪዎች እና መምህራን ያለምንም ወጪ በእነዚህ ኮርሶች በመመዝገብ ይህንን ልዩ የስልጠና እድል መጠቀም የሚችሉ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ውስጥ በመሳተፍና ችሎታቸውን በማጎልበት በአለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ ተወዳዳሪ መሆን ይችላሉ።
በዚህ ስልጠና ተመዝግበውና የትምህርት ይዘቶቹን ተምረው ያጠናቀቁ ተሳታፊዎች በአለም አቀፍ ድርጅቶች እውቅና ያለው እና የስራ እድልን በእጅጉ ሊያሳድግ ከሚችለው Udacity የምስክር ወረቀት ያገኛሉ።
ትምህርት ሚኒስቴር በስልጠናው እንዴት መመዝገብና መሳተፍ እንደሚቻል የሚያሳዩ መመሪያዎችን በጽሁፍና በቪዲዮ አዘጋጅቷል። ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎችና መምህራን ይሄንን በበዙ ክፍያ ይሰጥ የነበረን ስልጠና መመሪያውን ተከትሎ ብቻ በመመዝገብ በነጻ መሰልጠን ትችላላችሁ።
የመመሪያውን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/-zSmhhD5qE4 ላይ በመግባት መመልከት የምትችሉ ሲሆን በምስል የተደገፈውን መመሪያም ከዚህ ፖስት ጋር አጋርተናል።
ይሄንን ጠቃሚና ነጻ የስልጠና እድል ፍላጎቱ ላላቸውና የትምህርት ዝግጅታቸው ከዚህ ስልጠና ጋር ለሚገናኝ ጓደኞቻችሁ፣ ወዳጅ ፣ ቤተሰባችሁ እንዲሁም ተማሪዎችና መምህራን በማጋራት ተጨቃሚ እንዲሆኑ አድርጉ።
Jul 26, 2024 137
National News

የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና

የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና

የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና

Jul 23, 2024 628
National News

የ2016 ዓ. ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና በሠላም መጠናቀቁ ተገለፀ።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና በሠላም መጠናቀቁን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በመላ ሀገሪቱ በወረቀትና በኦላይን ሲሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሰላም መጠናቀቁን ገልፀዋል።
በዚህም ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 701,749 ተማሪዎች ውስጥ 684,372 ተማሪዎች ፈተናቸውን መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ ፈተናው በሰላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጻኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። ሙሉ መግለጫውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ። rb.gy/u17yql
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና በሠላም መጠናቀቁን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በመላ ሀገሪቱ በወረቀትና በኦላይን ሲሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሰላም መጠናቀቁን ገልፀዋል።
በዚህም ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 701,749 ተማሪዎች ውስጥ 684,372 ተማሪዎች ፈተናቸውን መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ ፈተናው በሰላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጻኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። ሙሉ መግለጫውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ። rb.gy/u17yql
Jul 19, 2024 622
National News

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞችን አበረታቱ።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ በአብርሆት ቤተመጻህፍትና በመነን ትምህርት ቤት መፈተኛ ጣቢያዎች በመገኘት የፈተና እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል። ተፈታኝ ተማሪዎችንም አበረታተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ከሐምሌ 03 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን በመፈተን ማስጀምሩ ይታወሳል። ይሄው አገር አቀፍ ፈተና ሁለተኛውን ዙር ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም በተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የቀጠለ ሲሆን በትግራይ ክልል በአሮጌው ካሪኩለም የሚፈተኑ ተማሪዎች በነገው እለት ሲያጠናቀቁ የሌሎች ክልሎች ተፈታኞች በዛሬው እለት የሚጨርሱ ይሆናል።
ክብርት ወ/ሮ አየለች ጉብኝቱን ባደረጉት ወቅት ለፈተናው የተደረገው ዘርፈብዙ ዝግጅትና ውጤት የተቋማት ትብብር የፈጠረው ውጤታማነት መሆኑን ገልጸዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ በአብርሆት ቤተመጻህፍትና በመነን ትምህርት ቤት መፈተኛ ጣቢያዎች በመገኘት የፈተና እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል። ተፈታኝ ተማሪዎችንም አበረታተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ከሐምሌ 03 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን በመፈተን ማስጀምሩ ይታወሳል። ይሄው አገር አቀፍ ፈተና ሁለተኛውን ዙር ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም በተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የቀጠለ ሲሆን በትግራይ ክልል በአሮጌው ካሪኩለም የሚፈተኑ ተማሪዎች በነገው እለት ሲያጠናቀቁ የሌሎች ክልሎች ተፈታኞች በዛሬው እለት የሚጨርሱ ይሆናል።
ክብርት ወ/ሮ አየለች ጉብኝቱን ባደረጉት ወቅት ለፈተናው የተደረገው ዘርፈብዙ ዝግጅትና ውጤት የተቋማት ትብብር የፈጠረው ውጤታማነት መሆኑን ገልጸዋል።
Jul 18, 2024 329
National News

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር ውይይት አደረጉ

የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር በትምህርት ዘርፉ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል። በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ከሀገራቸው የትምህርት ሚኒስቴር፣ ትምህርትን ከሚደግፉ የልማት ድርጅቶች ጋር በመተባበር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የኢትዮጵያን የትምህርት ሪፎርም ለመደገፍ በተለይም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የት/ቤቶችን መስፋፋትና እድሳት፣ የት/ቤት ምገባ ለማገዝና እና የተለያዩ የመምህራን ክህሎት ማሻሻያ ስልጠናዎች ለመስጠት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት በዩኒቨርስቲዎች መካከል በሚደረግ ትብብር፣ በነጻ ትምህርት እድል፣ በጋራ የምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር በትምህርት ዘርፉ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል። በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ከሀገራቸው የትምህርት ሚኒስቴር፣ ትምህርትን ከሚደግፉ የልማት ድርጅቶች ጋር በመተባበር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የኢትዮጵያን የትምህርት ሪፎርም ለመደገፍ በተለይም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የት/ቤቶችን መስፋፋትና እድሳት፣ የት/ቤት ምገባ ለማገዝና እና የተለያዩ የመምህራን ክህሎት ማሻሻያ ስልጠናዎች ለመስጠት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት በዩኒቨርስቲዎች መካከል በሚደረግ ትብብር፣ በነጻ ትምህርት እድል፣ በጋራ የምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
Jul 18, 2024 244
National News

ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈታናን አስጀመሩ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በአብርሆት ቤተ-መጽሃፍት በመገኘት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ብሄራዊ ፈተናን አስጀምረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በዚህ ዓመት እየተተገበረ ያለው የወረቀትና የኦን ላይን ፈተና (hybrid exam) መሆኑን አመልክተዋል። ለወደፊቱ ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን መፈተን ሲቻል የበለጠ ፈተናውን ከስርቆትና ከመኮራረጅ ከመታደጉም በላይ ለትምህርት ጥራት የበኩሉን ድርሻ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ፈተናውን ለማስተዳደር፣ ለቁጥጥር፣ ለህትመት፣ ለማጓጓዝ፣ ለሴኩዩሪቲ እና መሰል ወጭዎችን ለመቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በመጨረሻም የፈተናውን ድባብ ለማበላሸት ሀሰተኛ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ስለሚንሸራሸሩ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ አሳስበው ተማሪዎችም ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲሰሩ መክረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በአብርሆት ቤተ-መጽሃፍት በመገኘት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ብሄራዊ ፈተናን አስጀምረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በዚህ ዓመት እየተተገበረ ያለው የወረቀትና የኦን ላይን ፈተና (hybrid exam) መሆኑን አመልክተዋል። ለወደፊቱ ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን መፈተን ሲቻል የበለጠ ፈተናውን ከስርቆትና ከመኮራረጅ ከመታደጉም በላይ ለትምህርት ጥራት የበኩሉን ድርሻ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ፈተናውን ለማስተዳደር፣ ለቁጥጥር፣ ለህትመት፣ ለማጓጓዝ፣ ለሴኩዩሪቲ እና መሰል ወጭዎችን ለመቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በመጨረሻም የፈተናውን ድባብ ለማበላሸት ሀሰተኛ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ስለሚንሸራሸሩ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ አሳስበው ተማሪዎችም ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲሰሩ መክረዋል።
Jul 10, 2024 927
National News

ጠንካራ የጥናትና ምርምር የአስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የጥናትና ምርምር አስተዳደራዊ የአሰራር ስርዓቶችን በማጠናከርና በመገንባት ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አበባ ከሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲና Ohio State University ጋር በመተባበር ለሁሉም የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች ምክትል ፕሬዝዳንቶች ስልጠና እየሠጠ ነው።
ስልጠናው በምርምር ተቋማት ውስጥ ጠንካራ የጥናትና ምርምር አስተዳደራዊ ስርዓት መዘርጋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
በመርሃ ግብሩበ ማስጀመሪያ ላይ በመገኘት ቁልፍ መልእክት ያስተላለፍት የትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ስርጸት ዴስክ ሀላፊ ዶ/ር ሠራዊት ሀንዲሶ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥናትና ምርምር ስነ ምግባር ጥሰቶችና ያልተገቡ ልምዶችን ጠንካራ የአስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት መከላከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዶ/ር ሠራዊት አያይዘው እንደገለጹት ጥናትና ምርምር በማድረግ ሂደት ውስጥ ተመራማሪዎች በቅድሚያ የጥናትና ምርምር መርሆች፣ህጎችና ደንቦችን በሚገባ መረዳት፣ ማክበርና ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኢምባሲ ካልቸራል ጉዳዬች ሀላፊ ሪያን ብሬደን በበኩላቸው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ጠንካራ የጥናትና ምርምር አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት የተቋማቱን ተወዳዳሪነት ማሣደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሀላፊው አያይዘው እንደገለጹት ጠንካራ የአስተዳር ስርዓት የተቋማቱን የውስጥ አቅም ለማጎልበትና ወደ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሸጋገር የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚያግዝ አብራርተዋል።
የተቋማቱ የስራ ሀላፊዎች በበኩላቸው ጠንካራ የጥናትና ምርምር አስተዳር በማስፈን ረገድ ያሉ ማነቆችን አንስተው ውይይት አድረገዋል።
በዚህም በጥናትና ምርምር እንዲሁም ሀብት በማፈላለግና በማመንጨት የሚሳተፉ ምሁራንን የሚያበረታታና የሚደግፍ የአሠራር ስርዓት መዘርጋት ተመራማሪዎችን በስራ ገበታቸው እንዲቆዩና እንዲተጉ የሚያግዝ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የጥናትና ምርምር አስተዳደራዊ የአሰራር ስርዓቶችን በማጠናከርና በመገንባት ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አበባ ከሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲና Ohio State University ጋር በመተባበር ለሁሉም የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች ምክትል ፕሬዝዳንቶች ስልጠና እየሠጠ ነው።
ስልጠናው በምርምር ተቋማት ውስጥ ጠንካራ የጥናትና ምርምር አስተዳደራዊ ስርዓት መዘርጋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
በመርሃ ግብሩበ ማስጀመሪያ ላይ በመገኘት ቁልፍ መልእክት ያስተላለፍት የትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ስርጸት ዴስክ ሀላፊ ዶ/ር ሠራዊት ሀንዲሶ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥናትና ምርምር ስነ ምግባር ጥሰቶችና ያልተገቡ ልምዶችን ጠንካራ የአስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት መከላከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዶ/ር ሠራዊት አያይዘው እንደገለጹት ጥናትና ምርምር በማድረግ ሂደት ውስጥ ተመራማሪዎች በቅድሚያ የጥናትና ምርምር መርሆች፣ህጎችና ደንቦችን በሚገባ መረዳት፣ ማክበርና ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኢምባሲ ካልቸራል ጉዳዬች ሀላፊ ሪያን ብሬደን በበኩላቸው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ጠንካራ የጥናትና ምርምር አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት የተቋማቱን ተወዳዳሪነት ማሣደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሀላፊው አያይዘው እንደገለጹት ጠንካራ የአስተዳር ስርዓት የተቋማቱን የውስጥ አቅም ለማጎልበትና ወደ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሸጋገር የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚያግዝ አብራርተዋል።
የተቋማቱ የስራ ሀላፊዎች በበኩላቸው ጠንካራ የጥናትና ምርምር አስተዳር በማስፈን ረገድ ያሉ ማነቆችን አንስተው ውይይት አድረገዋል።
በዚህም በጥናትና ምርምር እንዲሁም ሀብት በማፈላለግና በማመንጨት የሚሳተፉ ምሁራንን የሚያበረታታና የሚደግፍ የአሠራር ስርዓት መዘርጋት ተመራማሪዎችን በስራ ገበታቸው እንዲቆዩና እንዲተጉ የሚያግዝ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
Jul 09, 2024 501
National News

አንጋፋው፣ ስመጥሩና ራስ ገዝ የሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስመረቀ

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የዩኒቨርስቲው ቻንስለር ክቡር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው፣ ለትምህርት ማህበረሰቡ ንግግር አድርገዋል። ያስተላለፉትን መሉ መልዕክት ለማግኘት https://rb.gy/sthacb 

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የዩኒቨርስቲው ቻንስለር ክቡር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው፣ ለትምህርት ማህበረሰቡ ንግግር አድርገዋል። ያስተላለፉትን መሉ መልዕክት ለማግኘት  https://rb.gy/sthacb 

Jul 08, 2024 690
National News

ለ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ:- ከሐሰተኛ ወሬዎች ራሳችሁን እንድትጠብቁ ስለማስገንዘብ!

የትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ለመፈተን ዝግጅቱን አጠናቅቆ የተማሪዎችን የመፈተኛ ቀን እየተጠባበቀ ይገኛል።
ነገር ግን ፈተናውን አስመልክቶ የተሳሳቱ መልዕክቶች በየጊዜው ትክክለኛ የትምህርት ሚኒስቴር ባልሆኑ ገጾች እየተለቀቁ ይገኛሉ።
ስለሆነም ተማሪዎች፣ ወላጆችና አሳዳጊዎች ፈተናው ከዚህ ቀደም እንደተገለጸው በበይነ መረብና በወረቀት እንደተማሪዎች #የቀደመ ምርጫ መሰረት የሚካሄድ መሆኑን በመገንዘብ አስቀድማችሁ በወረቀት የመረጣችሁ ወደተመደባችሁበት ዩኒቨርስቲ፣ በበይነ መረብ የመረጣችሁም በተመደባችሁበት የፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንደምትወስዱ ለማስገንዘብ ይሄንን መልዕክት እናስተላልፋለን።
ውድ ተማሪዎች በምስሉ ላይ ከተገለጹት አይነት ሃሰተኛ ወሬዎች ራሳችሁን በመከላከል ለፈተናው የምታደርጉትን ዝግጅት እንድትቀጥሉ እያሳሰብን ለማንኛውም መረጃ የሚከተሉትን የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ ገጾች ብቻ እንድትከተሉ እናሳስባለን።
የትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ለመፈተን ዝግጅቱን አጠናቅቆ የተማሪዎችን የመፈተኛ ቀን እየተጠባበቀ ይገኛል።
ነገር ግን ፈተናውን አስመልክቶ የተሳሳቱ መልዕክቶች በየጊዜው ትክክለኛ የትምህርት ሚኒስቴር ባልሆኑ ገጾች እየተለቀቁ ይገኛሉ።
ስለሆነም ተማሪዎች፣ ወላጆችና አሳዳጊዎች ፈተናው ከዚህ ቀደም እንደተገለጸው በበይነ መረብና በወረቀት እንደተማሪዎች #የቀደመ ምርጫ መሰረት የሚካሄድ መሆኑን በመገንዘብ አስቀድማችሁ በወረቀት የመረጣችሁ ወደተመደባችሁበት ዩኒቨርስቲ፣ በበይነ መረብ የመረጣችሁም በተመደባችሁበት የፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንደምትወስዱ ለማስገንዘብ ይሄንን መልዕክት እናስተላልፋለን።
ውድ ተማሪዎች በምስሉ ላይ ከተገለጹት አይነት ሃሰተኛ ወሬዎች ራሳችሁን በመከላከል ለፈተናው የምታደርጉትን ዝግጅት እንድትቀጥሉ እያሳሰብን ለማንኛውም መረጃ የሚከተሉትን የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ ገጾች ብቻ እንድትከተሉ እናሳስባለን።
Jul 07, 2024 558
National News

ጥብቅ ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉ

 

ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል።
ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ እየቀረበ ያለው መረጃ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ መሆኑን እየገለጽን ፈተናው በሁለቱም በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ በድጋሜ እንገልጻለን።
በመሆኑም ተማሪዎች ይሄንኑ ተገንዝባችሁ ዝግጅታችሁን እንድትቀጥሉ ሆኖ ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ እንደተለመደው ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት እየሰራ መሆኑንና ለዚህም ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉን እናስገነዝባለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል።
ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ እየቀረበ ያለው መረጃ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ መሆኑን እየገለጽን ፈተናው በሁለቱም በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ በድጋሜ እንገልጻለን።
በመሆኑም ተማሪዎች ይሄንኑ ተገንዝባችሁ ዝግጅታችሁን እንድትቀጥሉ ሆኖ ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ እንደተለመደው ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት እየሰራ መሆኑንና ለዚህም ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉን እናስገነዝባለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
Jul 05, 2024 505
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለተሻለ ሃገራዊ ክብር፣ ነፃነት እና ሉዓላዊነት" በሚል ርዕሰ ጉዳይ በተዘጋጀው ሀገራዊ ሰነድ ላይ ዉይይት አደረጉ።

ተረጅነትና የአደጋ ስጋት ተጋላጭነትን በመቀነስና የውስጥ አቅምን በመገንባት ሀገራዊ ክብርና ሉዓላዊነትን ማስከበር እንደሚገባ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በውይይቱ ማስጀመሪያ ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሀገራችን በርካታ ተፈጥሯዊ እና የሰው ሀብት ዕምቅ ፀጋ ያላት ባለታሪክና ገናና ሀገር ሆና ሳለ የድህነት ተምሳሌት መሆኗ ሁላችንንም ላይ ቁጭት ሊፈትጥ እንደሚገባ ገልጸዋል።
ክቡር ሚንስትር ዴኤታው አክለው እንደገለጹት ሁሉም ዜጋ ከተረጅነት አመለካከት ወጥቶ በቁርጠኝነት በመስራት በህብረተሰቡ ላይ ሊከሰቱ ለሚችሉ አደጋዎች ተገቢ ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀት ያስፈልጋል ብለዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይልቃል ወንድሜነህ በበኩላቸው ሠነዱን አስመልክቶ ባደረጉት ገለጻ ሰባዊ ድጋፍ እና የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ የመንግስት ድርሻ ብቻ አለመሆኑን ገልጸው ለዚህ ስኬታማነት ሁሉም ዜጋ የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አብራርተዋ።
መንግስት የተለያዩ የቅድመ አደጋ መከላከል ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑም በሰነዱ የተገለፀ ሲሆን እያንዳንዱ ዜጋም ያሉትን መልካም አጋጣሚዎችን በመጠቀም በቅንጅት ለውጤት ተኮር ተግባራት መዘጋጀት እንዳለበትም አክለው ገልጸዋል።
የሃገር ሉዓላዊነት ማስጠበቅ የሁሉም ዜጋ ድርሻ መሆኑን ያነሱት ተሳታፊዎቹ እንደ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ዘርፉን በተመለከተ የተቀናጀ የረጅም እና የአጭር ጊዜ ስትራቴጂ ተነድፎ ሁሉም ሰራተኛ የስራዉ ዕቅድ አካል አድርጎ የሚሰራበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ በማጠቃለያው ላይ ተገልጿል።
ተረጅነትና የአደጋ ስጋት ተጋላጭነትን በመቀነስና የውስጥ አቅምን በመገንባት ሀገራዊ ክብርና ሉዓላዊነትን ማስከበር እንደሚገባ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በውይይቱ ማስጀመሪያ ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሀገራችን በርካታ ተፈጥሯዊ እና የሰው ሀብት ዕምቅ ፀጋ ያላት ባለታሪክና ገናና ሀገር ሆና ሳለ የድህነት ተምሳሌት መሆኗ ሁላችንንም ላይ ቁጭት ሊፈትጥ እንደሚገባ ገልጸዋል።
ክቡር ሚንስትር ዴኤታው አክለው እንደገለጹት ሁሉም ዜጋ ከተረጅነት አመለካከት ወጥቶ በቁርጠኝነት በመስራት በህብረተሰቡ ላይ ሊከሰቱ ለሚችሉ አደጋዎች ተገቢ ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀት ያስፈልጋል ብለዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይልቃል ወንድሜነህ በበኩላቸው ሠነዱን አስመልክቶ ባደረጉት ገለጻ ሰባዊ ድጋፍ እና የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ የመንግስት ድርሻ ብቻ አለመሆኑን ገልጸው ለዚህ ስኬታማነት ሁሉም ዜጋ የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አብራርተዋ።
መንግስት የተለያዩ የቅድመ አደጋ መከላከል ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑም በሰነዱ የተገለፀ ሲሆን እያንዳንዱ ዜጋም ያሉትን መልካም አጋጣሚዎችን በመጠቀም በቅንጅት ለውጤት ተኮር ተግባራት መዘጋጀት እንዳለበትም አክለው ገልጸዋል።
የሃገር ሉዓላዊነት ማስጠበቅ የሁሉም ዜጋ ድርሻ መሆኑን ያነሱት ተሳታፊዎቹ እንደ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ዘርፉን በተመለከተ የተቀናጀ የረጅም እና የአጭር ጊዜ ስትራቴጂ ተነድፎ ሁሉም ሰራተኛ የስራዉ ዕቅድ አካል አድርጎ የሚሰራበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባ በማጠቃለያው ላይ ተገልጿል።
Jun 29, 2024 357
National News

2ኛው አመታዊ አገር አቀፍ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ጉባኤ ተካሄደ

2ኛው አመታዊ አገር አቀፍ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ጉባኤ በትምህርት ሚኒስቴር፤ በፍትህ ሚኒስቴር፣ በጀርመን ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት እና በሴቭ ዘ ችልድረን አስተባባሪነት ተካሄዷል።
የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልእክት የተቀናጀና የተሻለ የፍልሰት አስተዳደር ሥርዓት ለመዘርጋት የፖሊሲ ግብዓት የሚያቀርብ በትምህርት ሚኒስቴር የሚመራ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ቡድን ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የጉባኤውም የተሽላ የፍልሰት አስተዳደር በመፍጠር ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ለመቆጣጠርና መደበኛ ፍልሰትን ለማበረታታት የሚያስችል የፖሊሲ ግብዓት ለማሰባሰብ የሚያግዝ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ስርጸት ዴስክ ሃላፊ ዶ/ር ሠራዊት ሃንዲሶ በትምህርት ሚኒስቴር የሚመራው የፍልሰት ጥናትና ምርምር ቡድን በሰዎች የመነገድ፣ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን መከላከል፤ ከስደት ተመላሾችን መልሶ ማቋቋም የሚያስችሉ የፖሊሲ ግብዓቶችን እያቀረበ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ኢ-መደበኛ ፍልሰትን መከላከል የሚያስችል ጥልቅ ጥናትና ምርምር በማከናወን የተቀናጀ የፍልሰት አስተዳደር ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሠራ መሆኑን ጥቅሰው የፍልሰት ጥናትና ምርምር ቡድን በተለይ ከስደት ተመላሾች ላይ ትኩረት በማድረግ "የት፤ ምን ተጠና" የሚለውን በመለየት የጥናት ውጤቶችን ለፖሊሲ አውጪዎችና ውሳኔ ሰጪዎች ግብዓት እንዲሆኑ እያቀረበ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
በጉባኤው በኢትዮጵያ 29 ፍልሰት የሚበዛባቸው ዞኖች፣ 14 የድንበር መውጫ በሮች፣ 135 መተላለፊያ ቦታዎች መኖራቸው ተመላክቷል፡፡
በመድረኩም ከ2010 ዓ.ም ወዲህ በተለያዩ ሀገራት በችግር ላይ የነበሩ 500 ሺህ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለስ መቻሉን እና በተያዘው የ2016 በጀት ዓመት ብቻ ከ300 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት እድል መሰጠቱ ተነስቷል፡፡
በጉባኤው ከጥናትና ምርምሮች በተጨማሪ ከፍልሰት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የፍትህ ሚኒቴር፣የሴቶችና ማህባራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የእቅድ አፈጻጸሞች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡
2ኛው አመታዊ አገር አቀፍ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ጉባኤ በትምህርት ሚኒስቴር፤ በፍትህ ሚኒስቴር፣ በጀርመን ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት እና በሴቭ ዘ ችልድረን አስተባባሪነት ተካሄዷል።
የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልእክት የተቀናጀና የተሻለ የፍልሰት አስተዳደር ሥርዓት ለመዘርጋት የፖሊሲ ግብዓት የሚያቀርብ በትምህርት ሚኒስቴር የሚመራ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ቡድን ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የጉባኤውም የተሽላ የፍልሰት አስተዳደር በመፍጠር ኢ-መደበኛ ፍልሰትን ለመቆጣጠርና መደበኛ ፍልሰትን ለማበረታታት የሚያስችል የፖሊሲ ግብዓት ለማሰባሰብ የሚያግዝ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ስርጸት ዴስክ ሃላፊ ዶ/ር ሠራዊት ሃንዲሶ በትምህርት ሚኒስቴር የሚመራው የፍልሰት ጥናትና ምርምር ቡድን በሰዎች የመነገድ፣ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን መከላከል፤ ከስደት ተመላሾችን መልሶ ማቋቋም የሚያስችሉ የፖሊሲ ግብዓቶችን እያቀረበ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ኢ-መደበኛ ፍልሰትን መከላከል የሚያስችል ጥልቅ ጥናትና ምርምር በማከናወን የተቀናጀ የፍልሰት አስተዳደር ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሠራ መሆኑን ጥቅሰው የፍልሰት ጥናትና ምርምር ቡድን በተለይ ከስደት ተመላሾች ላይ ትኩረት በማድረግ "የት፤ ምን ተጠና" የሚለውን በመለየት የጥናት ውጤቶችን ለፖሊሲ አውጪዎችና ውሳኔ ሰጪዎች ግብዓት እንዲሆኑ እያቀረበ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
በጉባኤው በኢትዮጵያ 29 ፍልሰት የሚበዛባቸው ዞኖች፣ 14 የድንበር መውጫ በሮች፣ 135 መተላለፊያ ቦታዎች መኖራቸው ተመላክቷል፡፡
በመድረኩም ከ2010 ዓ.ም ወዲህ በተለያዩ ሀገራት በችግር ላይ የነበሩ 500 ሺህ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለስ መቻሉን እና በተያዘው የ2016 በጀት ዓመት ብቻ ከ300 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት እድል መሰጠቱ ተነስቷል፡፡
በጉባኤው ከጥናትና ምርምሮች በተጨማሪ ከፍልሰት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የፍትህ ሚኒቴር፣የሴቶችና ማህባራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የእቅድ አፈጻጸሞች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡
Jun 27, 2024 197
National News

የ2016ዓ.ም የፋርማሲ የመዉጫ ፈተና (Exit Exam) ለተፈተናችሁ ተማሪዎች በሙሉ

ከሰኔ 14 እስከ 19 ቀን 2016 ዓ. ም በ 244 ፕሮግራሞች በ57 የመንግስትና በ124 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለነበሩ ተማሪዎች የመዉጫ ፈተና ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ለስድስት ቀናት የተሰጠው ፈተና ያለምንም እንከን የተጠናቀቀ ሲሆን ነገር ግን በመጨረሻው ቀን የተሰጠዉ የፋርማሲ ፈተና ብቻ የቴክኒክ ችግር አጋጥሞታል። ስለሆነው ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎቹ ፈተናውን በድጋሜ እንዲወስዱ አመቻችቷል።
በዚሁ መሰረት ፈተናው በድጋሜ ቅዳሜ ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት ከ 3:00 ሰአት ጀምሮ እና ከሰአት ከ 8:00 ሰአት ጀምሮ ስለሚሰጥ ለፈተናው ተቀምጣችሁ የነበራችሁ የፋርማሲ ተማሪዎች በተፈተናችሁበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ በመገኘት በድጋሜ የሚሰጠውን ፈተና እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡
ከሰኔ 14 እስከ 19 ቀን 2016 ዓ. ም በ 244 ፕሮግራሞች በ57 የመንግስትና በ124 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለነበሩ ተማሪዎች የመዉጫ ፈተና ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ለስድስት ቀናት የተሰጠው ፈተና ያለምንም እንከን የተጠናቀቀ ሲሆን ነገር ግን በመጨረሻው ቀን የተሰጠዉ የፋርማሲ ፈተና ብቻ የቴክኒክ ችግር አጋጥሞታል። ስለሆነው ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎቹ ፈተናውን በድጋሜ እንዲወስዱ አመቻችቷል።
በዚሁ መሰረት ፈተናው በድጋሜ ቅዳሜ ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት ከ 3:00 ሰአት ጀምሮ እና ከሰአት ከ 8:00 ሰአት ጀምሮ ስለሚሰጥ ለፈተናው ተቀምጣችሁ የነበራችሁ የፋርማሲ ተማሪዎች በተፈተናችሁበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ በመገኘት በድጋሜ የሚሰጠውን ፈተና እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡
Jun 27, 2024 3.1K
National News

በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዙሪያ ከጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ

በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች በዚህ ዓመት በሚሰጠው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ዙሪያ ከጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
ውይይቱን ያስጀመሩት በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚ/ር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴ እንደገለጹት የ12 ዓመታት ድካም መሰብሰቢያ የሆነው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ዙሪያ ውይይት ማድረግ ሊከሰቱ የሚችሉ ክፍተቶችን ለመድፈን ትልቅ እድል ይፈጥራል ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም የሀገራችን ትምህርት መልካም ባህላችንን የሚያሳድጉ፣ ለሀገርና ለህዝብ ፍቅር ያላቸው፣ ብዝሃነትን የሚቀበሉ፣ ሰብዓዊ መብቶችን የሚያከብሩ፣ ለሰው ልጅ ደህንነትና እኩልነት ፣ ለፍትህ እና ለሰላምዘብ የሚቆሙ፣ ሁለንተናዊ ስብዕናቸው የተሟላ ዜጎችን ለማፍራት አንዱ መንገድ ግልጽና ከኩረጃ ነጻ የሆነ ፈተናና ምዘና መስጠት ነው ብለዋል። ለዚህም ሁላችንም በምንችለው መጠን አቅማችንን አሟጠን ለስኬታማነቱ እንረባረብ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በውይይት መድረክ ላይ የተገኙት ክቡር የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በበኩላቸው የጸጥታ አካላት በሚመለከታቸው ሃላፊዎቸ በሚሰጥ መመሪያ መሰረት በሙሉ አቅም ተልዕኳቸውን በመፈጸም ሀገራዊ አለኝታነታቸውን ማሳየት ይኖርባቸዋል ብለዋል። የፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል መላኩ ፋንታ ደግሞ ይህ ስራ በቅንጅት የሚሰራ በመሆኑ ያለምንም ስህተት የተሰጠ ሀገራዊ ተልዕኮን መወጣት ይገባል በማለት በአጽንዖት አስገንዝበዋል።
በውይይቱም በርካታ ሀሳቦች ተነስተው የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ተሰብሳቢዎቹ በሚሰጣቸው መመሪያ መሰረት ተልዕኳቸውን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች በዚህ ዓመት በሚሰጠው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ዙሪያ ከጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
ውይይቱን ያስጀመሩት በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚ/ር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴ እንደገለጹት የ12 ዓመታት ድካም መሰብሰቢያ የሆነው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ዙሪያ ውይይት ማድረግ ሊከሰቱ የሚችሉ ክፍተቶችን ለመድፈን ትልቅ እድል ይፈጥራል ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም የሀገራችን ትምህርት መልካም ባህላችንን የሚያሳድጉ፣ ለሀገርና ለህዝብ ፍቅር ያላቸው፣ ብዝሃነትን የሚቀበሉ፣ ሰብዓዊ መብቶችን የሚያከብሩ፣ ለሰው ልጅ ደህንነትና እኩልነት ፣ ለፍትህ እና ለሰላምዘብ የሚቆሙ፣ ሁለንተናዊ ስብዕናቸው የተሟላ ዜጎችን ለማፍራት አንዱ መንገድ ግልጽና ከኩረጃ ነጻ የሆነ ፈተናና ምዘና መስጠት ነው ብለዋል። ለዚህም ሁላችንም በምንችለው መጠን አቅማችንን አሟጠን ለስኬታማነቱ እንረባረብ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በውይይት መድረክ ላይ የተገኙት ክቡር የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በበኩላቸው የጸጥታ አካላት በሚመለከታቸው ሃላፊዎቸ በሚሰጥ መመሪያ መሰረት በሙሉ አቅም ተልዕኳቸውን በመፈጸም ሀገራዊ አለኝታነታቸውን ማሳየት ይኖርባቸዋል ብለዋል። የፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል መላኩ ፋንታ ደግሞ ይህ ስራ በቅንጅት የሚሰራ በመሆኑ ያለምንም ስህተት የተሰጠ ሀገራዊ ተልዕኮን መወጣት ይገባል በማለት በአጽንዖት አስገንዝበዋል።
በውይይቱም በርካታ ሀሳቦች ተነስተው የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ተሰብሳቢዎቹ በሚሰጣቸው መመሪያ መሰረት ተልዕኳቸውን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
Jun 25, 2024 233