News

National News

በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓትን ወጥና ዲጂታላይዝድ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ።

የትምህርት ሚኒስቴር ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የክልልና ከተማ መስተዳድር የትምህርት መረጃ አስተዳደር ባለሙያዎች፣ ስራ ሀላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሠሩ ባሉ ስራዎች ላይ ምክክር አድርጓል።
በምክክር መድረኩ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ቁልፍ መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ይበልጣል አያሌው የትምህርት ዘርፉን የመረጃ አስተዳደር ስርዓት ለማዘመንና ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው በማያያዝም በመከናወን ላይ ያሉ ጅምር ስራዎችን በሚገባው ፍጥነት በማጠናቀቅ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመረጃ አስተዳደር ስርዓቱን ማዘመንና ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዘላለም አሰፋ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ ያለውን የመረጃ ሥርዓት ለማዘመን እና ዲጂታላይዝ ለማድረግ በርካታ ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን በዚህም መረጃን በሃላፊነት እና በተጠያቂነት በማድረስ ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማረም ጥረት እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
ከትምህርት ቤት ጀምሮ ያለውን የመረጃ ስርዓት በማዘመን፣ ጥራትና ታዓማኒነቱን በማስጠበቅ በወቅቱ ተደራሽ ለማድረግና ጥቅም ላይ ማዋል የሚደረገውን ጥረት ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።
የትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓትና የአይሲቲ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰብስብ ለማ በበኩላቸው በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች የመረጃ ስርዓቱን ወጥና ዲጂታላይዝድ በማድረግ በመረጃ አሰባሰብ አደረጃጀትና ትንተና ተደራሽነትን ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።
በምክክር መድረኩ መረጃ ኦን ላይን (online) ብቻ ሳይሆን ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ኦፍ ላይን (Off line ) እና በሌሎችም አማራጮች በቴክኖሎጂ እንዴት መጠቀምና ሪፖርት ማድረግ እንደሚቻል መመላከቱንም አቶ ሰብስብ ለማ አመላክተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የክልልና ከተማ መስተዳድር የትምህርት መረጃ አስተዳደር ባለሙያዎች፣ ስራ ሀላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሠሩ ባሉ ስራዎች ላይ ምክክር አድርጓል።
በምክክር መድረኩ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ቁልፍ መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ይበልጣል አያሌው የትምህርት ዘርፉን የመረጃ አስተዳደር ስርዓት ለማዘመንና ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው በማያያዝም በመከናወን ላይ ያሉ ጅምር ስራዎችን በሚገባው ፍጥነት በማጠናቀቅ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመረጃ አስተዳደር ስርዓቱን ማዘመንና ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዘላለም አሰፋ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፉ ያለውን የመረጃ ሥርዓት ለማዘመን እና ዲጂታላይዝ ለማድረግ በርካታ ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን በዚህም መረጃን በሃላፊነት እና በተጠያቂነት በማድረስ ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማረም ጥረት እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
ከትምህርት ቤት ጀምሮ ያለውን የመረጃ ስርዓት በማዘመን፣ ጥራትና ታዓማኒነቱን በማስጠበቅ በወቅቱ ተደራሽ ለማድረግና ጥቅም ላይ ማዋል የሚደረገውን ጥረት ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።
የትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓትና የአይሲቲ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰብስብ ለማ በበኩላቸው በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች የመረጃ ስርዓቱን ወጥና ዲጂታላይዝድ በማድረግ በመረጃ አሰባሰብ አደረጃጀትና ትንተና ተደራሽነትን ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።
በምክክር መድረኩ መረጃ ኦን ላይን (online) ብቻ ሳይሆን ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ኦፍ ላይን (Off line ) እና በሌሎችም አማራጮች በቴክኖሎጂ እንዴት መጠቀምና ሪፖርት ማድረግ እንደሚቻል መመላከቱንም አቶ ሰብስብ ለማ አመላክተዋል።
Mar 07, 2025 167
National News

ዩኒቨርሲቲዎች ነፃ ምሁራዊ ውይይት የሚካሄድባቸው የሀገር የሀሳብና የእውቀት መሪ ሊሆኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ አሳሰቡ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ አመራሮችና ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ተልዕኳቸውን በሚገባ እንዲወጡ ከመንደር አስተሳሰብና ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በነፃነት እውነተኛ ምሁራዊ ውይይት የሚደረግባቸው የዚች ሀገር እውቀት መሪ ሊሆኑ ይገባል፤ ወደዛ እንዲሄዱም እንፈልጋለን ያሉ ሲሆን፤
ዩኒቨርሲቲዎች ትክክልና ስህተትን የሚለዩ ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ ምሩቃንን የሚያፈሩ እንዲሁም ሙስናን የሚቃወሙና የሚከላከሉ ሊሆኑም እንደሚገባም አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ሪሶርስ በአግባቡ ለመጠቀም የቅድሚያ ትኩረት ጉዳዮችን ለይተው በመስራት ችግሮችን ደረጃ በደረጃ መፍታት ይጠበቅባቸዋል ፤
በዚህም አዲሱ አመራር የትምህርት ጥራት የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይኖርበታልም ብለዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ(ዶ/ር) በተቋሙ የታዩ ጠንካራና መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች ለውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የዩኒቨርስቲው አዲስ አመራሮች ተቋሙን ካለበት ችግር ለማውጣት ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው አብራርተዋል።
የዩኒቨርስቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ታደሰ ረጋሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋሙን ለመለወጥ ከሁሉም አመራርና በለድርሻ ጋር በመግባባት ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልፀዋል።
የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላትም የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የአመራር ለውጥ ከተደረገላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ አመራሮችና ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አካሂደዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ተልዕኳቸውን በሚገባ እንዲወጡ ከመንደር አስተሳሰብና ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በነፃነት እውነተኛ ምሁራዊ ውይይት የሚደረግባቸው የዚች ሀገር እውቀት መሪ ሊሆኑ ይገባል፤ ወደዛ እንዲሄዱም እንፈልጋለን ያሉ ሲሆን፤
ዩኒቨርሲቲዎች ትክክልና ስህተትን የሚለዩ ጥሩ ሥነ-ምግባር የተላበሱ ምሩቃንን የሚያፈሩ እንዲሁም ሙስናን የሚቃወሙና የሚከላከሉ ሊሆኑም እንደሚገባም አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ሪሶርስ በአግባቡ ለመጠቀም የቅድሚያ ትኩረት ጉዳዮችን ለይተው በመስራት ችግሮችን ደረጃ በደረጃ መፍታት ይጠበቅባቸዋል ፤
በዚህም አዲሱ አመራር የትምህርት ጥራት የሚያረጋግጡ ሥራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይኖርበታልም ብለዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ(ዶ/ር) በተቋሙ የታዩ ጠንካራና መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች ለውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የዩኒቨርስቲው አዲስ አመራሮች ተቋሙን ካለበት ችግር ለማውጣት ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው አብራርተዋል።
የዩኒቨርስቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ታደሰ ረጋሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋሙን ለመለወጥ ከሁሉም አመራርና በለድርሻ ጋር በመግባባት ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልፀዋል።
የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላትም የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የአመራር ለውጥ ከተደረገላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
Mar 07, 2025 127
National News

የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነቱን ለማረጋገጥ የሚካሄዱ ስራዎች የሁሉንም የልማት አጋሮችና ባለድርሻዎች የጋራ ተሳትፎና ርብርብ እንደሚጠይቁ ተጠቆመ፤ የሂዩማን ካፒታል (Human Capital) ፕሮጀክት መክፈቻና ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በትምህርት ሚኒስትር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነቱን ለማረጋገጥ የሁሉንም የልማት አጋሮችና ባለድርሻዎች ቅንጅት ፣ ተሳትፎና ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት ትምህርትን ለማዳረስ በተሰሩ ስራዎች የተሻለ አፈፃፀም ቢኖርም የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ አኳያ አሁንም ሰፊ ክፍተት መኖሩን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ተናግረዋል።፡
በትምህርት ለትውልድ መርሃ ግብር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሳደግ፣ የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማትና ሌሎችም አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ስፋትና ጥልቀት ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል።
የሁዩማን ካፒታልረ ፕሮጀክቱ በ65 ወረዳወች እንደሚተገበር የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ፕሮጀክቱን በመደገፍ ላይ ለሚገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የዓለም ባንክና ለሌሎችም ባለድርሻዎች ምስጋና አቅርበዋል።፡
በመድረኩ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በሚካሄድባቸው ወረዳዎች የሚፈለገው ውጤት እንዲመዘገብ በትኩረትና በውጤታማነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዓለም ባንክ የፕሮጀክቱ ቲም ሊደር የሆኑት ሚስተር ሳመር ኤ አይ ሳመራይ በበኩላቸው የዓለም ባንክ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በመርሃ ግበብሩ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ፣ሴክተር መስሪያ ቤቶች የስራ ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙዎች ፣ ከዓለም ባንክና ከ65 ወረዳዎች የተወከሉ ተሳታፊዎች ተገኘተዋል።
በትምህርት ሚኒስትር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነቱን ለማረጋገጥ የሁሉንም የልማት አጋሮችና ባለድርሻዎች ቅንጅት ፣ ተሳትፎና ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት ትምህርትን ለማዳረስ በተሰሩ ስራዎች የተሻለ አፈፃፀም ቢኖርም የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ አኳያ አሁንም ሰፊ ክፍተት መኖሩን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ተናግረዋል።፡
በትምህርት ለትውልድ መርሃ ግብር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሳደግ፣ የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማትና ሌሎችም አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ስፋትና ጥልቀት ማሳደግ እንደሚገባም ገልጸዋል።
የሁዩማን ካፒታልረ ፕሮጀክቱ በ65 ወረዳወች እንደሚተገበር የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ፕሮጀክቱን በመደገፍ ላይ ለሚገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የዓለም ባንክና ለሌሎችም ባለድርሻዎች ምስጋና አቅርበዋል።፡
በመድረኩ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በሚካሄድባቸው ወረዳዎች የሚፈለገው ውጤት እንዲመዘገብ በትኩረትና በውጤታማነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዓለም ባንክ የፕሮጀክቱ ቲም ሊደር የሆኑት ሚስተር ሳመር ኤ አይ ሳመራይ በበኩላቸው የዓለም ባንክ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በመርሃ ግበብሩ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና ምክትል ኃላፊዎች ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ፣ሴክተር መስሪያ ቤቶች የስራ ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙዎች ፣ ከዓለም ባንክና ከ65 ወረዳዎች የተወከሉ ተሳታፊዎች ተገኘተዋል።
Mar 06, 2025 133
National News

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ግምቢ ከተማ ለሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መሠረት ድጋይ ተቀመጠ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ግምቢ ከተማ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መሠረት ድጋይ አስቀምጠዋል።
ሚኒስትሩ የግንባታውን ማስጀመሪያ መሠረት ድንጋይ ባስቀመጡበት ወቅትም የኢትዮጵያን ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል እየተወሰዱ ካሉ እርምጃዎች ውስጥ አንዱ የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል መሆኑን ተናግረዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት እየሠራ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ዛሬ የግንባታ ማስጀመሪያ መሠረት ድንጋይ የተቀመጠው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታም በአጭር ጊዜ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ስራውን እንዲጀምር ይደረጋልም ብለዋል።
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ደረጃቸው የተሻሻሉና መሠረተ ልማታቸው የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶችን መገንባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን አብራርተዋል።
የዞኑ አመራሮች በበኩላቸው የትምህርት ቤቱ ግንባታ በመጀመሩ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው ግንባታው እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።
ከዚም በተጨማሪ ሚኒስትሩና አመራሮቹ በጊንቢ ከተማ በሚገኙት ቢፍቱ ግምቢ እና ሴና ግምቢ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመገኘት ያለውን የመማር ማስተማር ሂደት በመመልከት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ግምቢ ከተማ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መሠረት ድጋይ አስቀምጠዋል።
ሚኒስትሩ የግንባታውን ማስጀመሪያ መሠረት ድንጋይ ባስቀመጡበት ወቅትም የኢትዮጵያን ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል እየተወሰዱ ካሉ እርምጃዎች ውስጥ አንዱ የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል መሆኑን ተናግረዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት እየሠራ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ዛሬ የግንባታ ማስጀመሪያ መሠረት ድንጋይ የተቀመጠው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታም በአጭር ጊዜ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ስራውን እንዲጀምር ይደረጋልም ብለዋል።
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ደረጃቸው የተሻሻሉና መሠረተ ልማታቸው የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶችን መገንባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን አብራርተዋል።
የዞኑ አመራሮች በበኩላቸው የትምህርት ቤቱ ግንባታ በመጀመሩ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው ግንባታው እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።
ከዚም በተጨማሪ ሚኒስትሩና አመራሮቹ በጊንቢ ከተማ በሚገኙት ቢፍቱ ግምቢ እና ሴና ግምቢ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመገኘት ያለውን የመማር ማስተማር ሂደት በመመልከት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
Mar 06, 2025 99
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ኘሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን በመጎብኘት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በጉብኝታቸውም ገተማ ሁለተኛ ደረጃ እና የነጌሶ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤትን ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች አሁን ያሉበት ደረጃ የቀጣይ ህይወታቸው የሚወሰንበት በመሆኑ ጠንክራችሁ መማር ይጠበቅባችኋል፤ በፍፁም በጊዜ መቀለድ የለባችሁም ሲሉም አሳስበዋል።
ይህ ሀገር እንዲቀጥል የወደፊቱ ሀገር ተረካቢዎች እናንተ በመሆናችሁ በቀለም ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባርም የተመሰገናችሁ ልትሆኑ ይገባል ብለዋል።
አክለውም የሚቀጥለውን ትውልድ በመቅረፅ ረገድ ትልቁ ድርሻ የመምህሩ መሆኑን በማንሳት መምህራን የተሰጣቸውን ኃላፊነት በሚገባ እንዲወጡም ጠይቀዋል።
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተማሪዎች የዓመቱ ትምህርት በአግባቡ ስለማይሸፈንላቸውና ስታንዳርዱን የጠበቀ የክፍል ፈተና ስለማይወስዱ መጨረሻ እየተቸገሩ መሆኑን ጠቅሰው መምህራን በዚህ ረገድ ትኩረት ሰጥተው መስራትና ተማሪዎች ተገቢውን እውቀት ይዘው ከክፍል ክፍል እንዲዛወሩ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አመራሮቹ በትምህርት ቤቶቹ በነበራቸው ጉብኝት ሰላማዊ የመማር ማስተማር ስራ እየተከናወነ እንደሆነና ተማሪዎችም ተረጋግተው እየተማሩ መሆኑን መመልከት መቻላቸውን ገልፀዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ኘሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን በመጎብኘት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በጉብኝታቸውም ገተማ ሁለተኛ ደረጃ እና የነጌሶ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤትን ተመልክተዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች አሁን ያሉበት ደረጃ የቀጣይ ህይወታቸው የሚወሰንበት በመሆኑ ጠንክራችሁ መማር ይጠበቅባችኋል፤ በፍፁም በጊዜ መቀለድ የለባችሁም ሲሉም አሳስበዋል።
ይህ ሀገር እንዲቀጥል የወደፊቱ ሀገር ተረካቢዎች እናንተ በመሆናችሁ በቀለም ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባርም የተመሰገናችሁ ልትሆኑ ይገባል ብለዋል።
አክለውም የሚቀጥለውን ትውልድ በመቅረፅ ረገድ ትልቁ ድርሻ የመምህሩ መሆኑን በማንሳት መምህራን የተሰጣቸውን ኃላፊነት በሚገባ እንዲወጡም ጠይቀዋል።
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተማሪዎች የዓመቱ ትምህርት በአግባቡ ስለማይሸፈንላቸውና ስታንዳርዱን የጠበቀ የክፍል ፈተና ስለማይወስዱ መጨረሻ እየተቸገሩ መሆኑን ጠቅሰው መምህራን በዚህ ረገድ ትኩረት ሰጥተው መስራትና ተማሪዎች ተገቢውን እውቀት ይዘው ከክፍል ክፍል እንዲዛወሩ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አመራሮቹ በትምህርት ቤቶቹ በነበራቸው ጉብኝት ሰላማዊ የመማር ማስተማር ስራ እየተከናወነ እንደሆነና ተማሪዎችም ተረጋግተው እየተማሩ መሆኑን መመልከት መቻላቸውን ገልፀዋል።
Mar 06, 2025 104
National News

ዩኒቨርሲቲዎች እውነተኛ የመማሪያ፣ የማስተማሪያ እንዲሁም ጥናትና ምርምሮች የሚሰሩባቸው ትክክለኛ የእውቀት መፈለጊያ ሰላማዊ ቦታዎች ሊሆኑ ይገባል። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትሩ ኘሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወለጋ ዩኒቨርስቲ በመገኘት ከዩኒቨርስቲው አመራሮችና ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል ።
በዚሁ ወቅት ዩኒቨርሲቲዎች እውነተኛ የመማሪያ፣ የማስተማሪያ እንዲሁም ጥናትና ምርምሮች የሚሰሩባቸው ትክክለኛ የእውቀት መፈለጊያ ሰላማዊ ቦታዎች ሊሆኑ ይገባል፤ ለዚህም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎሮም ሥራዎች አላማ ይህን ለማሳካት መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም የዩኒቨርሲቲዎችን አስተዳደር፣ አስተሳሰብና አጠቃላይ ባህል መቀየር አስፈላጊ በመሆኑ የዩኒቨርቲውን አመራር የመቀየር ሥራ መሰራቱን ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች የአካባቢያቸውን ፀጋ በመለየት ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ የህብረተሰቡን ህይወት መቀየር እና ለሀገራቸው ችግር መፍትሔ መፈለግ ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን በዚህ ረገድ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደራዊ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) በዩኒቨርሲቲው በተደረገ ሱፐርቪዥን በጥንካሬና መሻሻል ያለባቸውን ተብለው የተለዩ ጉዳዮችን ለውይይት መነሻ አቅርበዋል።
በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት አዲስ የተመደበው አመራር የተጀመሩ ሥራዎችን በሚገባ በመፈተሽ የትምህርት ጥራትን የሚያረጋግጡ ጉዳዮችን ቅድሚያ በመስጠት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ተስፋዬ ለማ (ዶ/ር) በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው መገኘት ተገቢውን ድጋፍ ለማድረግና ተጠያቂነትን ለማስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀው ዪኒቨርሲቲው የአመራር ለውጥ ከተደረገለት በኋላ የትምህርት ጥራት ፕሮግራሞች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን ተልዕኮ በሚገባው መጠንና ጥራት ለማሳደግ አስተሳሰባችንና አሰራራችንን በማሻሻል ያለንን አቅም አሟጠን መጠቀም ይጠበቅብናልም ብለዋል።
አመራሮቹ በነቀምቴ ከተማ በነበራቸው ቆይታ የዩኒቨርሲቲውን ኮምፕሬንሲቭ ሆስፒታል ጨምሮ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ኘሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወለጋ ዩኒቨርስቲ በመገኘት ከዩኒቨርስቲው አመራሮችና ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል ።
በዚሁ ወቅት ዩኒቨርሲቲዎች እውነተኛ የመማሪያ፣ የማስተማሪያ እንዲሁም ጥናትና ምርምሮች የሚሰሩባቸው ትክክለኛ የእውቀት መፈለጊያ ሰላማዊ ቦታዎች ሊሆኑ ይገባል፤ ለዚህም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎሮም ሥራዎች አላማ ይህን ለማሳካት መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም የዩኒቨርሲቲዎችን አስተዳደር፣ አስተሳሰብና አጠቃላይ ባህል መቀየር አስፈላጊ በመሆኑ የዩኒቨርቲውን አመራር የመቀየር ሥራ መሰራቱን ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች የአካባቢያቸውን ፀጋ በመለየት ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ የህብረተሰቡን ህይወት መቀየር እና ለሀገራቸው ችግር መፍትሔ መፈለግ ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን በዚህ ረገድ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደራዊ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) በዩኒቨርሲቲው በተደረገ ሱፐርቪዥን በጥንካሬና መሻሻል ያለባቸውን ተብለው የተለዩ ጉዳዮችን ለውይይት መነሻ አቅርበዋል።
በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት አዲስ የተመደበው አመራር የተጀመሩ ሥራዎችን በሚገባ በመፈተሽ የትምህርት ጥራትን የሚያረጋግጡ ጉዳዮችን ቅድሚያ በመስጠት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ተስፋዬ ለማ (ዶ/ር) በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው መገኘት ተገቢውን ድጋፍ ለማድረግና ተጠያቂነትን ለማስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀው ዪኒቨርሲቲው የአመራር ለውጥ ከተደረገለት በኋላ የትምህርት ጥራት ፕሮግራሞች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን ተልዕኮ በሚገባው መጠንና ጥራት ለማሳደግ አስተሳሰባችንና አሰራራችንን በማሻሻል ያለንን አቅም አሟጠን መጠቀም ይጠበቅብናልም ብለዋል።
አመራሮቹ በነቀምቴ ከተማ በነበራቸው ቆይታ የዩኒቨርሲቲውን ኮምፕሬንሲቭ ሆስፒታል ጨምሮ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
Mar 06, 2025 120
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲት የህክምና ፋካልቲ ተማሪዎች ምረቃ ያደረጉት ሙሉ ንግግር ፤

ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤ https://moe.gov.et/resources/others/5

ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤ https://moe.gov.et/resources/others/5

Mar 05, 2025 70
National News

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናትና ምርምሮች ተገቢውን ሥነ-ምግባር የተከተሉና የህብረተሰቡን ችግሮ የሚፈቱ ሊሆኑ እንደሚገባ ተጠቆመ።

በትምህርት ሚኒስቴር በጥናትና ምርምር ሥነ ምግባር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ለመንግስትና ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሰጥቷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በሀገራችን የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ በርካታ ጥናትና ምርምሮች ቢሰሩም ህብረተሰቡ ላይ ያመጡት ለውጥ ግን የሚጠበቀውን ያክል አይደለም ብለዋል።
እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንዳልሂነም ገልጸዋል።
ጥራት ያለው ጥናት ለመስራትና ለሳይንስ ያለን እይታ እንዲጨምር የምንፈልግ ከሆነ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
በዚህም የሚሰሩ ምርምሮች ተገቢውን ስነምግባር የተከተሉ፣ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሊሆኑ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፍርሞችን ቀርፆ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም በመንግስትም ሆነ በግል ተቋማት የሚሰሩ ጥናትና ምርምሮች ከመመረቂያነት ባለፈ ጥራት ያላቸው ችግር ፈቺ እንዲሆኑ ለማድረግና ወጥ የሆነ አሰራር ሥርዓትን ለመከተል እንዲቻል ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
በስልጠናው ከመንግስትና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተወከሉ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር በጥናትና ምርምር ሥነ ምግባር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ለመንግስትና ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሰጥቷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በሀገራችን የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ በርካታ ጥናትና ምርምሮች ቢሰሩም ህብረተሰቡ ላይ ያመጡት ለውጥ ግን የሚጠበቀውን ያክል አይደለም ብለዋል።
እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንዳልሂነም ገልጸዋል።
ጥራት ያለው ጥናት ለመስራትና ለሳይንስ ያለን እይታ እንዲጨምር የምንፈልግ ከሆነ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
በዚህም የሚሰሩ ምርምሮች ተገቢውን ስነምግባር የተከተሉ፣ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሊሆኑ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፍርሞችን ቀርፆ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም በመንግስትም ሆነ በግል ተቋማት የሚሰሩ ጥናትና ምርምሮች ከመመረቂያነት ባለፈ ጥራት ያላቸው ችግር ፈቺ እንዲሆኑ ለማድረግና ወጥ የሆነ አሰራር ሥርዓትን ለመከተል እንዲቻል ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
በስልጠናው ከመንግስትና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተወከሉ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።
Mar 01, 2025 62
National News

በተለያዩ ክልሎች የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃትና ተነሳሽነት ለማሳደግ ስልጠናዎች እየተሰጡ ነው።

በሁሉም ክልሎች በተመረጡ የስልጠና ማዕከላት እተሰጠ ያለው ስልጠና በስነ-ልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ፣ በስራና ተግባር ተኮር ትምህርት እና በአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርት ማስተማር ስነ ዘዴ ላይ ያተኮረ ነው፡፡
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ ስልጠና ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት ችግሮች በነበሩባቸው አካባቢዎች ለሚያስተምሩ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እየተሰጠ ያለው ስልጠና መምህራን ተግዳሮቶችን ተቋቁመው የማስተማርና ስራቸውን በአግባቡ መምራት እንዲችሉ እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ለስልጠናው ትልቅ ስራ እየሰራ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ቶላ ከስልጠናው ባሻገም ሚኒስቴሩ ሞተር ብስክሌቶችን በመለገስ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መጽሃፍት ሙሉ በሙሉ አሳትሞ በማሰራጨት፣ ሞዴል ትምህርት ቤቶችን በመገንባትና በሌሎችም የትምህርትን ጥራት ለማስጠበቅ እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች እያደረገ ላለው ድጋፍ አመስግነዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመተባበር የተለያዩ አጫጭርና የረዥም ጊዜ ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ለመምህራንና ለትምህርት አመራሮች የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ/ Psycho-Social Support/ ስልጠና የሚሰጠው ስልጠና ዓላማ መምህራንና የትምህርት አመራሮች በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያቶች የሚፈጠሩ ችግሮችን ተቋቁመው ማስተማር እንዲችሉ ለመደገፍ መሆኑን አስረድተዋል፡።
የመምህራን ትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ አሰግድ ሜሬሳ በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች የመፈጸምና ማስፈጸም አቅም ለማሳደግ አጫጭር የስራ ላይ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በአገር አቀፍ ደረጃ ከ6 ሺህ በላይ ለሚሆኑ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች የመፈጸምና ማስፈጸም አቅማቸውን ማሳደግ የሚያስችል አጫጭር የስራ ላይ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ወ/ሮ አሰገደች አስታውቀዋል፡፡
ስልጠናዎቹ በስራና ተግባር ትምህርት ማስተማር ስነ ዘዴ፣ በስነ-ልቦና፣ የአእምሮ ጤና እና ማህበራዊ ድጋፍ ፣ በመጀመሪያ ቋንቋ ለሚያስተምሩ መምህራን ቋንቋን የማስተማር ስነዘዴ፣ በተከታታይ ምዘና አሰጣጥ፣ በትምህርት ዕቅድ ዝግጅትና ዲጂታል ቴክኖሎጂን መጠቀም ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑንም አብራርተዋል።
በሁሉም ክልሎች በተመረጡ የስልጠና ማዕከላት እተሰጠ ያለው ስልጠና በስነ-ልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ፣ በስራና ተግባር ተኮር ትምህርት እና በአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርት ማስተማር ስነ ዘዴ ላይ ያተኮረ ነው፡፡
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ ስልጠና ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት ችግሮች በነበሩባቸው አካባቢዎች ለሚያስተምሩ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እየተሰጠ ያለው ስልጠና መምህራን ተግዳሮቶችን ተቋቁመው የማስተማርና ስራቸውን በአግባቡ መምራት እንዲችሉ እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ለስልጠናው ትልቅ ስራ እየሰራ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ቶላ ከስልጠናው ባሻገም ሚኒስቴሩ ሞተር ብስክሌቶችን በመለገስ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መጽሃፍት ሙሉ በሙሉ አሳትሞ በማሰራጨት፣ ሞዴል ትምህርት ቤቶችን በመገንባትና በሌሎችም የትምህርትን ጥራት ለማስጠበቅ እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች እያደረገ ላለው ድጋፍ አመስግነዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመተባበር የተለያዩ አጫጭርና የረዥም ጊዜ ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ለመምህራንና ለትምህርት አመራሮች የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ/ Psycho-Social Support/ ስልጠና የሚሰጠው ስልጠና ዓላማ መምህራንና የትምህርት አመራሮች በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ምክንያቶች የሚፈጠሩ ችግሮችን ተቋቁመው ማስተማር እንዲችሉ ለመደገፍ መሆኑን አስረድተዋል፡።
የመምህራን ትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ አሰግድ ሜሬሳ በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች የመፈጸምና ማስፈጸም አቅም ለማሳደግ አጫጭር የስራ ላይ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በአገር አቀፍ ደረጃ ከ6 ሺህ በላይ ለሚሆኑ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች የመፈጸምና ማስፈጸም አቅማቸውን ማሳደግ የሚያስችል አጫጭር የስራ ላይ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ወ/ሮ አሰገደች አስታውቀዋል፡፡
ስልጠናዎቹ በስራና ተግባር ትምህርት ማስተማር ስነ ዘዴ፣ በስነ-ልቦና፣ የአእምሮ ጤና እና ማህበራዊ ድጋፍ ፣ በመጀመሪያ ቋንቋ ለሚያስተምሩ መምህራን ቋንቋን የማስተማር ስነዘዴ፣ በተከታታይ ምዘና አሰጣጥ፣ በትምህርት ዕቅድ ዝግጅትና ዲጂታል ቴክኖሎጂን መጠቀም ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑንም አብራርተዋል።
Mar 01, 2025 62
National News

የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች 129ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከበሩ፡፡

«ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል! » በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ129ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመርሃ- ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች ድልና የነጻነት አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች ለይቻላል መንፈሰ ማጎለበቻነት በመጠቀም በያዝናቸው የሥራ ዘርፎች ላይ የሚጠበቅብንን ስኬት ማስመዘግብ እንደሚገባ ተናገግረዋል፡፡
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጨምረውም የአድዋን ድል ከማክበርና ቱሩፋቶቹንም ከመጠቀም በተጨማሪ እኛ መሥራት ያለብንን የቤት ሥራ በወቅቱ በማከናወን የሀገራችን ልማት ማፋጠን ይኖርብናል ብለዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከቅድመ አያቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አንስተዋል፡፡
አቶ ኡመር አክለውም የአድዋ ድል ቅድመ አያቶቻችን ብሄራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ሀይማኖታቸው፣ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶቻቸው ሳይገድባቸው የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት ያስከበሩ መሆኑን አብራርተው አሁን ያለው ትውልድ ከዚህ መማር እንደሚገባው ገለጸዋል።
«ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል! » በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ129ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመርሃ- ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች ድልና የነጻነት አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች ለይቻላል መንፈሰ ማጎለበቻነት በመጠቀም በያዝናቸው የሥራ ዘርፎች ላይ የሚጠበቅብንን ስኬት ማስመዘግብ እንደሚገባ ተናገግረዋል፡፡
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጨምረውም የአድዋን ድል ከማክበርና ቱሩፋቶቹንም ከመጠቀም በተጨማሪ እኛ መሥራት ያለብንን የቤት ሥራ በወቅቱ በማከናወን የሀገራችን ልማት ማፋጠን ይኖርብናል ብለዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከቅድመ አያቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አንስተዋል፡፡
አቶ ኡመር አክለውም የአድዋ ድል ቅድመ አያቶቻችን ብሄራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ሀይማኖታቸው፣ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶቻቸው ሳይገድባቸው የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት ያስከበሩ መሆኑን አብራርተው አሁን ያለው ትውልድ ከዚህ መማር እንደሚገባው ገለጸዋል።
Feb 28, 2025 65
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከፊንላንድ አምባሳደር ጋር ተወያዩ፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከፊንላንድ አምባሳደር ሲኒካ አንቲላ ጋር ተወይተዋል፡፡
በዚሁ ጊዜ ፊንላንድ ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በጥራትና በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድርግ የሄደችበት መንገድ በሞዴልነት የሚወሰድ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል፡፡
አክለውም በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን እና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ በሪፎርሙ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል፡፡
በዚህም በትምህርት ዘርፉ የሪፎርም ሥራዎች ድጋፍ የሚያደርጉ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ የትምህርት አጋር ድርጅቶች ገንዘባቸው በትክክል ለታለመለት ዓላማ መዋሉን በሚያረጋግጥ እና የትምህርት ሚኒስቴርን የሪፎርም እቅዶች ለማሳካት በሚያስችል መልኩ በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የፊንላንድ አምባሳደር ሲኒካ አንቲላ በበኩላቸው በትምህርቱ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር በርካታ ሥራዎችን በትብብር መስራታቸውን አንስተው ይህንን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡
በተለይም በመምህራን የአቅም ግንባታ፣ ልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት፣በቴክኖሎጂ ፈጠራ እና በሌሎችም የትምህርት ዘርፎች በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የሚደረጉ ማናቸውም ድጋፎች በትክክል የህጻናትን የመማር ሁኔታ በሚያመቻቹና ጥራትን በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ እንዲሆኑ ተስማምተዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከፊንላንድ አምባሳደር ሲኒካ አንቲላ ጋር ተወይተዋል፡፡
በዚሁ ጊዜ ፊንላንድ ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በጥራትና በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድርግ የሄደችበት መንገድ በሞዴልነት የሚወሰድ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል፡፡
አክለውም በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን እና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ በሪፎርሙ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል፡፡
በዚህም በትምህርት ዘርፉ የሪፎርም ሥራዎች ድጋፍ የሚያደርጉ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ የትምህርት አጋር ድርጅቶች ገንዘባቸው በትክክል ለታለመለት ዓላማ መዋሉን በሚያረጋግጥ እና የትምህርት ሚኒስቴርን የሪፎርም እቅዶች ለማሳካት በሚያስችል መልኩ በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የፊንላንድ አምባሳደር ሲኒካ አንቲላ በበኩላቸው በትምህርቱ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር በርካታ ሥራዎችን በትብብር መስራታቸውን አንስተው ይህንን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡
በተለይም በመምህራን የአቅም ግንባታ፣ ልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት፣በቴክኖሎጂ ፈጠራ እና በሌሎችም የትምህርት ዘርፎች በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የሚደረጉ ማናቸውም ድጋፎች በትክክል የህጻናትን የመማር ሁኔታ በሚያመቻቹና ጥራትን በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ እንዲሆኑ ተስማምተዋል፡፡
Feb 25, 2025 43
National News

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ የማድረግ ሂደት የሁሉንም ባለድርሻዎች ድጋፍና ትብብር እንደሚጠይቅ ተጠቆመ፤

በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ አስተዳደር ስትራተጂክ እቅድ እና ሴኔት ህግ ለማዳበር የተዘጋጀ አውደ ጥናት በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው።
የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ አውደ ጥናቱን ሲከፍቱ እንደገለጹትት የዩኒቨርስቲዎችን የራስ ገዝ አስተዳደር ማስፋት የመንግስት አካላት ፣ የአካዳሚክ መሪዎች፣ የመምህራን ፣የተማሪዎችና የማህብረሰቡን ትብብር ይሻል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራስ -ገዝነት የተቋማቱን ራስን በራስ የማስተዳደርና አካዳሚያዊ ነጻነትን በማረጋገጥ የትምህርት ጥራት ምርምርና ፈጠራን በውጤታማነትና በብቃት ለመፈጸም እንደሚያስችል ክቡር አቶ ኮራ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ በበኩላቸው የአውደ ጥናቱ ዓላማ ወደ ራስገዝነት ሽግግር ለሚያርጉ የመንግስት ዩኒቨርሰቲዎች ወሳኝ የሆኑ ስትራቴጂክ እቅድና ሴኔት ህግ ለማዳበር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
አውደ ጥናቱ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራትን ለመደገፍ የአሜሪካ መንግስት ገንዘብ ድጋፍ ማድረጉንም ፕሮፌሰር በላይ አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው ድጋፉ በኢትዮጵያና በአሜሪካ መንግስታት መካከል ያለው ድጋፍና ትብብር አካል መሆኑን ተናግረዋል፡
በኢትዮጵና በአሜሪካ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከከል የቆዬ የአካዳሚክና ምርምር ልውውጥ መኖሩን የጠቆሙት አምባሳደሩ ያሁኑ ድጋፍ ዘጠኝ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራስ ገዝ ለመሆን የሚያደርጉትን ሂደት እንደሚያግዝም ጠቅሰዋል።
የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሰለሞን አብርሃ በበኩላቸው ዘጠኝ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችሉ የዝግጅት ስራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ አስረድተዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የመቀሌ፣ የጎንደር ፣ የባህርዳር፣ የአዲስ አበባ ሳንስና ቴክኖሎጂ፣ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ የሀዋሳ ፣ የጅማ፣ የሐረማያ እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶችና የሚመለከታቸው ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ አስተዳደር ስትራተጂክ እቅድ እና ሴኔት ህግ ለማዳበር የተዘጋጀ አውደ ጥናት በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው።
የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ አውደ ጥናቱን ሲከፍቱ እንደገለጹትት የዩኒቨርስቲዎችን የራስ ገዝ አስተዳደር ማስፋት የመንግስት አካላት ፣ የአካዳሚክ መሪዎች፣ የመምህራን ፣የተማሪዎችና የማህብረሰቡን ትብብር ይሻል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራስ -ገዝነት የተቋማቱን ራስን በራስ የማስተዳደርና አካዳሚያዊ ነጻነትን በማረጋገጥ የትምህርት ጥራት ምርምርና ፈጠራን በውጤታማነትና በብቃት ለመፈጸም እንደሚያስችል ክቡር አቶ ኮራ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ በበኩላቸው የአውደ ጥናቱ ዓላማ ወደ ራስገዝነት ሽግግር ለሚያርጉ የመንግስት ዩኒቨርሰቲዎች ወሳኝ የሆኑ ስትራቴጂክ እቅድና ሴኔት ህግ ለማዳበር መሆኑን አስረድተዋል፡፡
አውደ ጥናቱ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ ለማድረግ የተጀመሩ ተግባራትን ለመደገፍ የአሜሪካ መንግስት ገንዘብ ድጋፍ ማድረጉንም ፕሮፌሰር በላይ አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው ድጋፉ በኢትዮጵያና በአሜሪካ መንግስታት መካከል ያለው ድጋፍና ትብብር አካል መሆኑን ተናግረዋል፡
በኢትዮጵና በአሜሪካ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከከል የቆዬ የአካዳሚክና ምርምር ልውውጥ መኖሩን የጠቆሙት አምባሳደሩ ያሁኑ ድጋፍ ዘጠኝ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራስ ገዝ ለመሆን የሚያደርጉትን ሂደት እንደሚያግዝም ጠቅሰዋል።
የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሰለሞን አብርሃ በበኩላቸው ዘጠኝ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችሉ የዝግጅት ስራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ አስረድተዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የመቀሌ፣ የጎንደር ፣ የባህርዳር፣ የአዲስ አበባ ሳንስና ቴክኖሎጂ፣ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ የሀዋሳ ፣ የጅማ፣ የሐረማያ እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶችና የሚመለከታቸው ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
Feb 25, 2025 38
National News

አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ የትምህርቱ ዘርፉ ለሚያደርገው ሪፎርም አቅም እንደሚሆን ተጠቆመ፤ በአዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።

በውይይት ላይ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ ይህ አዋጅ በዚህ መንገድ ሲዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው የትምህርት ዘርፉ አሁን ለደረሰበት ደረጃ በሚመጥን ነው ብለዋል። አዋጁን ለማስፈጸም ከክልልና፣ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎችና ከሚመለከታቸው የትምህርት ሴክተሩ ባለሙያዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ አሳታፊ በሆነ መልኩ በቀጣይ ደንብና መመሪያ እንደሚዘጋጅም ገልጸዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም የትምህርት አዋጁ ለሴክሩ የሚኖረውን ፋይዳ ሲያብራሩ የትምህርት አካታችነትን፣ ተደራሽኝነትን፣ ፍትሃዊነትንና ጥራትን ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው ብለዋል። ይህ አዋጁ ለሚደረገው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም አቅም እንደሚሆን ጠቁመው የዜጎችን የመማር መብት የሚያረጋግጥና ሀላፊነትና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ መሆኑን ተናገረዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የስርዓተ-ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ቴዎድሮስ ሽዋርገጥ እንደገለጹት ደግሞ አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ የመንግስት ዘርፉን ብቻ ሳይሆን የግል ዘርፉንም የሚያበረታታ መሆኑን ተናገረው አዋጁ ወደትግበራ ሲገባ በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ አወንታዊ ለውጥ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
በውይይቱ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች፣ የትምህርት ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች በውይይቱ ተሳታፊ ሆነዋል።
በውይይት ላይ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ ይህ አዋጅ በዚህ መንገድ ሲዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው የትምህርት ዘርፉ አሁን ለደረሰበት ደረጃ በሚመጥን ነው ብለዋል። አዋጁን ለማስፈጸም ከክልልና፣ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎችና ከሚመለከታቸው የትምህርት ሴክተሩ ባለሙያዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ አሳታፊ በሆነ መልኩ በቀጣይ ደንብና መመሪያ እንደሚዘጋጅም ገልጸዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም የትምህርት አዋጁ ለሴክሩ የሚኖረውን ፋይዳ ሲያብራሩ የትምህርት አካታችነትን፣ ተደራሽኝነትን፣ ፍትሃዊነትንና ጥራትን ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው ብለዋል። ይህ አዋጁ ለሚደረገው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም አቅም እንደሚሆን ጠቁመው የዜጎችን የመማር መብት የሚያረጋግጥና ሀላፊነትና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ መሆኑን ተናገረዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የስርዓተ-ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ቴዎድሮስ ሽዋርገጥ እንደገለጹት ደግሞ አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ የመንግስት ዘርፉን ብቻ ሳይሆን የግል ዘርፉንም የሚያበረታታ መሆኑን ተናገረው አዋጁ ወደትግበራ ሲገባ በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ አወንታዊ ለውጥ እንደሚኖረው ጠቁመዋል።
በውይይቱ የክልልና የከተማ አስተዳደሮች ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች፣ የትምህርት ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች በውይይቱ ተሳታፊ ሆነዋል።
Feb 22, 2025 40
National News

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ ነው፤

በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዘርፉ ውጤታማ ለመሆን የተናበበ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥራት ያለው ትምህርት በማግኘት ረገድ እኩል እድል እንዲኖረው ፤ በድሃና ሃብታም መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ ሥራ መስራት አለብን ብለዋል።
ይችን ሀገር መለወጥ የሚቻለው የትምህርት ሥርዓቱን መቀየር ሲቻል መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሩ በርካታ ሪፎርሞች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖር ማድረግ ላይ መሥራት እንደሚገባ አንስተው በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል የተጀመረው ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ከፈተና ጋር በተያያዘ በዚህ ዓመት 150 ሺ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን ባለው ሁኔታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የተማሪ መጽሐፍት አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉን ገልፀው የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተማሪ መጽሐፍ አንድ ለአንድ ያልደረሰ በመሆኑ ክልሎች በትኩረት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የመምህራንን አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከተመረቁ ዜጎች ውስጥ ልዩ የማስተማር ሙያ (pedagogy) ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ሙያው እንዲገቡ እንደሚደረግም ገልፀዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ይህ የምክክር መድረክ በዘርፉ ባለፉት ስድስት ወራት የተፈፀሙ ዋና ዋና ተግባራት ላይ የሚመክር መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ የሪፎርምና ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ላይ አንዱ ከአንዱ ተሞክሮ የሚወስድበት ፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና መፍትዎች ላይ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫ የሚቀመጥበት እንደሆነም አብራርተዋል።
በምክክር መድረኩ የክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዘርፉ ውጤታማ ለመሆን የተናበበ ሥራ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥራት ያለው ትምህርት በማግኘት ረገድ እኩል እድል እንዲኖረው ፤ በድሃና ሃብታም መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ ሥራ መስራት አለብን ብለዋል።
ይችን ሀገር መለወጥ የሚቻለው የትምህርት ሥርዓቱን መቀየር ሲቻል መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሩ በርካታ ሪፎርሞች ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖር ማድረግ ላይ መሥራት እንደሚገባ አንስተው በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል የተጀመረው ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ከፈተና ጋር በተያያዘ በዚህ ዓመት 150 ሺ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
አሁን ባለው ሁኔታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የተማሪ መጽሐፍት አንድ ለአንድ ማድረስ መቻሉን ገልፀው የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተማሪ መጽሐፍ አንድ ለአንድ ያልደረሰ በመሆኑ ክልሎች በትኩረት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የመምህራንን አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከተመረቁ ዜጎች ውስጥ ልዩ የማስተማር ሙያ (pedagogy) ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ሙያው እንዲገቡ እንደሚደረግም ገልፀዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ይህ የምክክር መድረክ በዘርፉ ባለፉት ስድስት ወራት የተፈፀሙ ዋና ዋና ተግባራት ላይ የሚመክር መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ የሪፎርምና ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ላይ አንዱ ከአንዱ ተሞክሮ የሚወስድበት ፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና መፍትዎች ላይ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫ የሚቀመጥበት እንደሆነም አብራርተዋል።
በምክክር መድረኩ የክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
Feb 20, 2025 36
Recent News
Follow Us