News

National News

የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ-ገዝ አድርጎ መልሶ በማቋቋም ሂደት ውስጥ ያሉ መልካም አጋጣሚዎችና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሄደ።

ምክክሩ በቀጣይ ራስ ገዝ ሆነው የሚቋቋሙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለሚያደርጉት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ግብዓት የሚሆኑ የሽግግር ረቂቅ መመሪያ ላይ ያተኮረ እንደሆነም ተመላክቷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መርሃ ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት በትምህርት ዘርፉ በመከናወን ላይ ያሉ የሪፎርም ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው አብራርተዋል።
የተቋማት ስኬትም ይሁን ውድቀት በዩኒቨርሲቲው አመራርና ማህበረሰብ ላይ የሚወድቅ መሆኑን በመገንዘብ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በቁርጠኝነት በማስፈጸም ዩኒቨርሲቲዎች ብቃት ያለው ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት የሚያስችሉ ተቋማት እንዲሆኑ ማድረግ እንደሚገባም አክለው ገልጸዋል።
በዚህም ረገድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረውን የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የማድረግ ሂደት የተገኙ ተሞክሮዎችና ተግዳሮቶችን በሚገባ በመለየት በመጪው አመት ራስ ገዝ ሆነው የሚቋቋሙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገጥማቸውን ጫና በመቋቋም ለእውነትና እውቀት የቆሙና የማይገፋ ጠንካራ ተቋም ሆነው ለመውጣት አስፈላጊውን ጥረት ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሀሳብ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ አድርጎ መልሶ የማቋቋም ሂደቶችና በራስ ገዝነት የሚገኙ ቱሩፋቶችን አንስተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባደረጉት ገለጻ ተቋማት ራስ ገዝ ሆነው ሲቋቋሙ የሀገርና የማህበረሰብ እምነትና አደራ ተጥሎባቸው መሆኑን በመረዳት የተቀመጡ ግቦችን ከስኬት ለማድረስ በጋራ መስራት እንደሚገባ አብራርተዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ ገዝነት ሽግግር የተዘጋጀውን ረቂቅ መመሪያ ለውይይት መነሻ አቅርበዋል።
ረቂቅ ሰነዱ ለራስ ገዝነት ሽግግር የሚያበቁ መስፈርቶችና ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችን የተካተተበት ሲሆን ዩኒቨርሲቲዎች በዚህ ረቂቅ መመሪያ እየተመዘኑ ሽግግር የሚያደርጉ በመሆኑ በተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው ማብራሪያና ምላሽ ተሠጥቶባቸዋል።
በቀጣይ ራስ ገዝ በመሆን ለሚቋቋሙ ዩኒቨርሲቲዎች ተሞክሮ እንዲሆን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግርን የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ወይይት ተደርጎበታል።
ምክክሩ በቀጣይ ራስ ገዝ ሆነው የሚቋቋሙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለሚያደርጉት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ግብዓት የሚሆኑ የሽግግር ረቂቅ መመሪያ ላይ ያተኮረ እንደሆነም ተመላክቷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መርሃ ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት በትምህርት ዘርፉ በመከናወን ላይ ያሉ የሪፎርም ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው አብራርተዋል።
የተቋማት ስኬትም ይሁን ውድቀት በዩኒቨርሲቲው አመራርና ማህበረሰብ ላይ የሚወድቅ መሆኑን በመገንዘብ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በቁርጠኝነት በማስፈጸም ዩኒቨርሲቲዎች ብቃት ያለው ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት የሚያስችሉ ተቋማት እንዲሆኑ ማድረግ እንደሚገባም አክለው ገልጸዋል።
በዚህም ረገድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረውን የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የማድረግ ሂደት የተገኙ ተሞክሮዎችና ተግዳሮቶችን በሚገባ በመለየት በመጪው አመት ራስ ገዝ ሆነው የሚቋቋሙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገጥማቸውን ጫና በመቋቋም ለእውነትና እውቀት የቆሙና የማይገፋ ጠንካራ ተቋም ሆነው ለመውጣት አስፈላጊውን ጥረት ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሀሳብ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ አድርጎ መልሶ የማቋቋም ሂደቶችና በራስ ገዝነት የሚገኙ ቱሩፋቶችን አንስተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባደረጉት ገለጻ ተቋማት ራስ ገዝ ሆነው ሲቋቋሙ የሀገርና የማህበረሰብ እምነትና አደራ ተጥሎባቸው መሆኑን በመረዳት የተቀመጡ ግቦችን ከስኬት ለማድረስ በጋራ መስራት እንደሚገባ አብራርተዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ ገዝነት ሽግግር የተዘጋጀውን ረቂቅ መመሪያ ለውይይት መነሻ አቅርበዋል።
ረቂቅ ሰነዱ ለራስ ገዝነት ሽግግር የሚያበቁ መስፈርቶችና ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችን የተካተተበት ሲሆን ዩኒቨርሲቲዎች በዚህ ረቂቅ መመሪያ እየተመዘኑ ሽግግር የሚያደርጉ በመሆኑ በተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው ማብራሪያና ምላሽ ተሠጥቶባቸዋል።
በቀጣይ ራስ ገዝ በመሆን ለሚቋቋሙ ዩኒቨርሲቲዎች ተሞክሮ እንዲሆን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግርን የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ወይይት ተደርጎበታል።
Dec 20, 2025 46
National News

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተደረገላቸው አቀባበል

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተደረገላቸው አቀባበል

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተደረገላቸው አቀባበል

Dec 20, 2025 40
National News

በኢትዮጵያና ህንድ መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ አስታወቁ። ‎የሦስተኛ ዲግሪ ነጻ የትምህርት እድል ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።

የከፍተኛ የትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ወዳጅነትና ትብብር እየተጠናከረ በመሄድ ላይ ነው።
‎ይፋ የሆነው የድህረ ምረቃ ትምህርትና ምርምር መርሃ ግብርም የድህረ ምረቃ ትምህርት አቅም በመገንባት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትልቅ ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ከህንድ የቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጠው የትምህርት እድል፣ የምርምር፣ ቴክኖሎጅና ፈጠራን በማሳደግ ብቁ የሰው ሀይል በጥራት ማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
‎የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው የመርሃ ግብሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን የሦስተኛ ዲግሪ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።
‎በህንድ ካሉ 8 የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በየዓመት 250 በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ 1,250 ተማሪዎች ነጻ የዶክተሬት ትምህርት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ኤባ ጠቅሰዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው የፕሮግራም አስተዳደርና አፈጻጸምን በተመለከተ በቀጣይ ከሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ጋር ምክክርና የመረጃ ልውውጥ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ በበይነ መረብ የተሳተፉት ስምንት (😎 የህንድ ቴክኖሎጂ ተቋማት ስለተቋሞቻቸውና በሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ስልጠና ስለ የሚሰጡባቸው ፕሮግራሞች አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።
የከፍተኛ የትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ወዳጅነትና ትብብር እየተጠናከረ በመሄድ ላይ ነው።
‎ይፋ የሆነው የድህረ ምረቃ ትምህርትና ምርምር መርሃ ግብርም የድህረ ምረቃ ትምህርት አቅም በመገንባት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትልቅ ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ከህንድ የቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጠው የትምህርት እድል፣ የምርምር፣ ቴክኖሎጅና ፈጠራን በማሳደግ ብቁ የሰው ሀይል በጥራት ማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
‎የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው የመርሃ ግብሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን የሦስተኛ ዲግሪ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።
‎በህንድ ካሉ 8 የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በየዓመት 250 በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ 1,250 ተማሪዎች ነጻ የዶክተሬት ትምህርት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ኤባ ጠቅሰዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው የፕሮግራም አስተዳደርና አፈጻጸምን በተመለከተ በቀጣይ ከሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ጋር ምክክርና የመረጃ ልውውጥ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ በበይነ መረብ የተሳተፉት ስምንት (😎 የህንድ ቴክኖሎጂ ተቋማት ስለተቋሞቻቸውና በሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ስልጠና ስለ የሚሰጡባቸው ፕሮግራሞች አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።
Dec 20, 2025 29
National News

በኢትዮጵያና ህንድ መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ አስታወቁ። ‎የሦስተኛ ዲግሪ ነጻ የትምህርት እድል ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።

የከፍተኛ የትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ወዳጅነትና ትብብር እየተጠናከረ በመሄድ ላይ ነው።
‎ይፋ የሆነው የድህረ ምረቃ ትምህርትና ምርምር መርሃ ግብርም የድህረ ምረቃ ትምህርት አቅም በመገንባት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትልቅ ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ከህንድ የቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጠው የትምህርት እድል፣ የምርምር፣ ቴክኖሎጅና ፈጠራን በማሳደግ ብቁ የሰው ሀይል በጥራት ማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
‎የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው የመርሃ ግብሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን የሦስተኛ ዲግሪ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።
‎በህንድ ካሉ 8 የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በየዓመት 250 በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ 1,250 ተማሪዎች ነጻ የዶክተሬት ትምህርት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ኤባ ጠቅሰዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው የፕሮግራም አስተዳደርና አፈጻጸምን በተመለከተ በቀጣይ ከሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ጋር ምክክርና የመረጃ ልውውጥ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ በበይነ መረብ የተሳተፉት ስምንት (😎 የህንድ ቴክኖሎጂ ተቋማት ስለተቋሞቻቸውና በሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ስልጠና ስለ የሚሰጡባቸው ፕሮግራሞች አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።
የከፍተኛ የትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ወዳጅነትና ትብብር እየተጠናከረ በመሄድ ላይ ነው።
‎ይፋ የሆነው የድህረ ምረቃ ትምህርትና ምርምር መርሃ ግብርም የድህረ ምረቃ ትምህርት አቅም በመገንባት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትልቅ ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ከህንድ የቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጠው የትምህርት እድል፣ የምርምር፣ ቴክኖሎጅና ፈጠራን በማሳደግ ብቁ የሰው ሀይል በጥራት ማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
‎የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው የመርሃ ግብሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን የሦስተኛ ዲግሪ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።
‎በህንድ ካሉ 8 የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በየዓመት 250 በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ 1,250 ተማሪዎች ነጻ የዶክተሬት ትምህርት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ኤባ ጠቅሰዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው የፕሮግራም አስተዳደርና አፈጻጸምን በተመለከተ በቀጣይ ከሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ጋር ምክክርና የመረጃ ልውውጥ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ በበይነ መረብ የተሳተፉት ስምንት (😎 የህንድ ቴክኖሎጂ ተቋማት ስለተቋሞቻቸውና በሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ስልጠና ስለ የሚሰጡባቸው ፕሮግራሞች አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።
Dec 20, 2025 39
Advertisement

ማስታወቂያ

ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎችና ደንብ ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ በ3 የተለያዩ ጉዳዮች ማለትም፤
1. በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የትምህርት ሚኒስቴር የጎልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ፕሮግራም አፈፃጸም ረቂቅ መመሪያ ሊንክ: - https://forms.gle/RXsuSUGtFFYrkAMQ9
2. የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርትና ስልጠና ምክር ቤት ማቋቋሚያ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት ረቂቅ ደንብ ሊንክ: - https://forms.gle/TZTSPZrJzgEnY2Rq9
3. የተፋጠነ ትምህርት መርሃ-ግብር አፈፃጸም ረቂቅ መመሪያ ሊንክ: - https://forms.gle/16CDaGfzkXDF6fwt6 አዘጋጅቷል።
በመሆኑም ሰነዶቹን በማንበብ አስተያየት እንድትሰጡ እየጠየቅን፤
 ለመጀመር ከእያንዳንዱ ረቂው መመሪያ/ ደንብ ፊት ለፊት ያሉትን ሊንኮች መጫን፤
 በመቀጠል ማስፈንጠሪያ የሚለውን በመጫን ሰነዱን ማግኘት ትችላላችሁ፣
 ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ (submit) የሚለውን በመጫን መረጃውን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎችና ደንብ ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ በ3 የተለያዩ ጉዳዮች ማለትም፤
1. በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የትምህርት ሚኒስቴር የጎልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ፕሮግራም አፈፃጸም ረቂቅ መመሪያ ሊንክ: - https://forms.gle/RXsuSUGtFFYrkAMQ9
2. የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርትና ስልጠና ምክር ቤት ማቋቋሚያ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት ረቂቅ ደንብ ሊንክ: - https://forms.gle/TZTSPZrJzgEnY2Rq9
3. የተፋጠነ ትምህርት መርሃ-ግብር አፈፃጸም ረቂቅ መመሪያ ሊንክ: - https://forms.gle/16CDaGfzkXDF6fwt6 አዘጋጅቷል።
በመሆኑም ሰነዶቹን በማንበብ አስተያየት እንድትሰጡ እየጠየቅን፤
 ለመጀመር ከእያንዳንዱ ረቂው መመሪያ/ ደንብ ፊት ለፊት ያሉትን ሊንኮች መጫን፤
 በመቀጠል ማስፈንጠሪያ የሚለውን በመጫን ሰነዱን ማግኘት ትችላላችሁ፣
 ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ (submit) የሚለውን በመጫን መረጃውን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
Dec 15, 2025 33
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ከቻይና የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከቻይና የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የቻይና የቋንቋ ትምህርትና ትብብር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር Yu Yunfeng ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ የቻይና ስትራቴጂክ አጋር ናት ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ በኢንቨስትመንት ረገድ ከምታደርገው ትብብር በተጨማሪ የቻይና ቋንቋ ትምህርት በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን በሌሎች የትምህርት ተቋማት በማስፋፋት የቻይና ቋንቋን ማስተማር እንደሚፈልጉ ገልጸውላቸዋል።
ይህም ዜጎች በርካታ ቋንቋዎችን እንዲያውቁ ከማድረጉም ባሻገር የህዝብ ለህዝብ ትብብርን የበለጠ በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ቻይና ለረጅም ጊዜ የቆየ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸውና የብሪክስ አባል ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው አሁን ባለው የኢትዮጵያና የቻይና ግንኙነት የቻይና ቋንቋ በኢትዮጵያ የትምህርት ተቋማት ቢሰጥ ለዜጎች ጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል።
በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ የቋንቋ ትምህርትን በተመለከተ በግልጽ የተቀመጡ ጉዳዮችን ለልዑካን ቡድኑ ያብራሩት ክቡር ሚኒስትሩ በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረውን የቻይና ቋንቋ ትምህርት በሌሎች የትምህርት ተቋማት ለማስፋፋት ፍላጎቶች እንዳሉና አተገባበሩን በተመለከተ ውይይት ማድረግ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
አያይዘውም በዚህ ዓመት የመማር ማስተማር በሚጀመርባቸው አምስት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቻይና ቋንቋን ለማስተማር በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ፍላጎት እንዳለ በማንሳት የቻይና ቋንቋ መምህራንን እንዲመደቡ የልዑካን ቡድኑን ጠይቀዋል።
ሁለቱ አካላት በውይይታቸውም በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚሰጠውን የቻይና ቋንቋ ትምህርትን በተመለከተ የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ መዘጋጀት እንዳለበት እና በሌሎች የትምህርት ተቋማት ለመተግበር እንዲቻል የሥርዓተ ትምህርት፣ የመጽሃፍት እና የመምህራን አቅርቦትን በተመለከተ አስቀድሞ መወያየት እንደሚገባ አንስተዋል።
በመጨረሻም በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ስምምነት የተደረሰባቸውን ጉዳዮች ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ዝርዝር የስምምነት ሰነድ ከሁለቱ አካላት በተውጣጣ ኮሚቴ እንዲዘጋጅ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከቻይና የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የቻይና የቋንቋ ትምህርትና ትብብር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር Yu Yunfeng ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ የቻይና ስትራቴጂክ አጋር ናት ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ በኢንቨስትመንት ረገድ ከምታደርገው ትብብር በተጨማሪ የቻይና ቋንቋ ትምህርት በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን በሌሎች የትምህርት ተቋማት በማስፋፋት የቻይና ቋንቋን ማስተማር እንደሚፈልጉ ገልጸውላቸዋል።
ይህም ዜጎች በርካታ ቋንቋዎችን እንዲያውቁ ከማድረጉም ባሻገር የህዝብ ለህዝብ ትብብርን የበለጠ በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ቻይና ለረጅም ጊዜ የቆየ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸውና የብሪክስ አባል ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው አሁን ባለው የኢትዮጵያና የቻይና ግንኙነት የቻይና ቋንቋ በኢትዮጵያ የትምህርት ተቋማት ቢሰጥ ለዜጎች ጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል።
በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ የቋንቋ ትምህርትን በተመለከተ በግልጽ የተቀመጡ ጉዳዮችን ለልዑካን ቡድኑ ያብራሩት ክቡር ሚኒስትሩ በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረውን የቻይና ቋንቋ ትምህርት በሌሎች የትምህርት ተቋማት ለማስፋፋት ፍላጎቶች እንዳሉና አተገባበሩን በተመለከተ ውይይት ማድረግ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
አያይዘውም በዚህ ዓመት የመማር ማስተማር በሚጀመርባቸው አምስት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቻይና ቋንቋን ለማስተማር በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ፍላጎት እንዳለ በማንሳት የቻይና ቋንቋ መምህራንን እንዲመደቡ የልዑካን ቡድኑን ጠይቀዋል።
ሁለቱ አካላት በውይይታቸውም በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚሰጠውን የቻይና ቋንቋ ትምህርትን በተመለከተ የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ መዘጋጀት እንዳለበት እና በሌሎች የትምህርት ተቋማት ለመተግበር እንዲቻል የሥርዓተ ትምህርት፣ የመጽሃፍት እና የመምህራን አቅርቦትን በተመለከተ አስቀድሞ መወያየት እንደሚገባ አንስተዋል።
በመጨረሻም በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ስምምነት የተደረሰባቸውን ጉዳዮች ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ዝርዝር የስምምነት ሰነድ ከሁለቱ አካላት በተውጣጣ ኮሚቴ እንዲዘጋጅ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
Dec 05, 2025 409
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ ከደቡብ አፍሪካ የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይትም University of South Africa (UNISA) በኢትዮጵያ እንዴት በትብብር መስራት እንደሚችል ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የUnisa’s Principal and Vice-Chancellor Prof Puleng LenkaBula ፤ UNISA ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ከ2006 ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ መስክ በርካታ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ሲያስመርቅ መቆየቱን ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከፍተኛ ችግር የነበረበትና በከፍተኛ ትምህርት ዜጎች ዲግሪ በገንዘብ የሚገዙበት ጭምር የነበረ በመሆኑ፤
ይህንን ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የትምህርት ጥራትን ሊያረጋግጡ እንዲሁም ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ መሆኑና በዚህም ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ዓለም በፈጣን እድገት ላይ ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ በጣም ውስብስብ እየሆነች መጥታለች ያሉት ሚኒስትሩ UNISA ከ20 ዓመት በፊት በጀመረው ስምምነትና ፕሮግራም መሰረት አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፍላጎትና የኢኮኖሚ እድገት ሊቀጥል የማይችል በመሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያስችል መልኩ መታየት እንዳለበት አስገንዝበው በአፍሪካ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮች ይህንን መሰረት ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ሥራዎችም ሀገራችን ለያዘቻቸው የልማት እቅዶች መሳካት የሚያስፈልግ የሰው ሃይል ልማትን በሚያግዙ የትምህርት መስኮች እንደ ማዕድን፣ ፔትሮ ኬሚካል፣ አግሮ ኢንደስትሪ የመሳሰሉት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን ይገባቸዋልም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው UNISA በሀገራችን ላለፉት 20 ዓመታት ሲሰራ መቆየቱ ቢታወቅም፣ በቀጣይ የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲስ ውይይት ማድረግ ይቻላል ብለዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየትኞቹ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት እንደሚቻል እንዲለዩና ለቀጣይ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲቀርቡ ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የUNISA ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አመራሮች ተግኝተዋል።
በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የUnisa’s Principal and Vice-Chancellor Prof Puleng LenkaBula ፤ UNISA ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ከ2006 ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ መስክ በርካታ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ሲያስመርቅ መቆየቱን ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከፍተኛ ችግር የነበረበትና በከፍተኛ ትምህርት ዜጎች ዲግሪ በገንዘብ የሚገዙበት ጭምር የነበረ በመሆኑ፤
ይህንን ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የትምህርት ጥራትን ሊያረጋግጡ እንዲሁም ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ መሆኑና በዚህም ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ዓለም በፈጣን እድገት ላይ ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ በጣም ውስብስብ እየሆነች መጥታለች ያሉት ሚኒስትሩ UNISA ከ20 ዓመት በፊት በጀመረው ስምምነትና ፕሮግራም መሰረት አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፍላጎትና የኢኮኖሚ እድገት ሊቀጥል የማይችል በመሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያስችል መልኩ መታየት እንዳለበት አስገንዝበው በአፍሪካ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮች ይህንን መሰረት ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ሥራዎችም ሀገራችን ለያዘቻቸው የልማት እቅዶች መሳካት የሚያስፈልግ የሰው ሃይል ልማትን በሚያግዙ የትምህርት መስኮች እንደ ማዕድን፣ ፔትሮ ኬሚካል፣ አግሮ ኢንደስትሪ የመሳሰሉት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን ይገባቸዋልም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው UNISA በሀገራችን ላለፉት 20 ዓመታት ሲሰራ መቆየቱ ቢታወቅም፣ በቀጣይ የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲስ ውይይት ማድረግ ይቻላል ብለዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየትኞቹ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት እንደሚቻል እንዲለዩና ለቀጣይ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲቀርቡ ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የUNISA ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አመራሮች ተግኝተዋል።
Nov 29, 2025 440
National News

እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስ በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም እቀፍ ህጻናት አድን ድርጅት ጋር በመተባበር” በኢትዮጵያ የፍልሰት ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሲቪክ ማህባራት፣መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ-ጥናት ተካሂዷል፡፡
በአውደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስቴር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስም ሆነ በሚገባ ለማስተዳደር በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻና አጋር አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
አውደ-ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች የጋራ ትብብርና ቅንጅት በሚሰሩ ምርምሮች የሚለዩ የህግ ማዕቀፎችና የአተገባበር ክፍተቶች አግባብነት ባላቸው ተቋማት ተወስደው ለአስፈጻሚዎች ውሳኔና ለፋጻሚዎች ትግበራ ማሻሻያነት የሚውሉበት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮፌሰር ክንደያ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለፍልሰት በተሰጠው ሀገራዊ ትኩረት የፍልሰት ምርምር ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት የምርምር ስትራጂዎች መካከል አንዱ እንዲሆን ከመደረጉ በተጨማሪ ፍልሰት እንደ አንድ ዋነኛ የማህበረሰብ አጀንዳ ተወሶዶ እንዲሰራበት መደረጉንም ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት የፕሮግራም ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ድርጅታቸው ለብሄራዊ ፍልሰት ምላሽ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከፍልሰት ምርምር የሚገኙ ግብዓቶች ደግሞ ፕሮግራሙ ይበልጥ በውጤታማነት እንዲፈጸም የሚያግዙ እቅዶችን ለማቀድ የሚረዱ በመሆናቸው ድርጅታቸው ምርምርን አጽዕኖት ሰጥቶ የሚደግፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት ባሉት የተለያዩ ችግሮች የተነሰ እየጨመሩ የመጡ የፍልሰት ተጋላጭነቶችንና ጉዳቶችን ለመቀንስ ቅንጅትና አስቸኳይ የጋራ ምላሾች የሚያስፈልጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር ብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብረሃም አያሌው ባለፉት ሦስት አመታት ፍልሰት ብሄራዊ የልማትና ደህንነት አጀንዳ ወደ መሆን የተሸጋገረ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህም በመሆኑ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በፍልሰት ላይ ያተኮረ የድህረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎች መክፈታቸውንና የተወሰኑት ደግሞ የፍልሰት ምርምር ማዕከላት ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀገራችን በዓለም አቀፍ፣ በአህጉርና በኢጋድ ሀገራት ደረጃ የተለያዩ የፍልሰት ስምምነቶችን ተቀብላ የህጎቿ አካል አድርጋ እየተገበረች መሆኗን ጠቅሰው ከጥቂት አመታት ወዲህ ለፍልሰት በተሰጠው ትኩረት ሀገራዊ የፍልሰት ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
በአውደ-ጥናቱ ላይ የተላያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ውጤታማነትና ለአውደ-ጥናቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም እቀፍ ህጻናት አድን ድርጅት ጋር በመተባበር” በኢትዮጵያ የፍልሰት ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሲቪክ ማህባራት፣መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ-ጥናት ተካሂዷል፡፡
በአውደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስቴር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስም ሆነ በሚገባ ለማስተዳደር በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻና አጋር አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
አውደ-ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች የጋራ ትብብርና ቅንጅት በሚሰሩ ምርምሮች የሚለዩ የህግ ማዕቀፎችና የአተገባበር ክፍተቶች አግባብነት ባላቸው ተቋማት ተወስደው ለአስፈጻሚዎች ውሳኔና ለፋጻሚዎች ትግበራ ማሻሻያነት የሚውሉበት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮፌሰር ክንደያ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለፍልሰት በተሰጠው ሀገራዊ ትኩረት የፍልሰት ምርምር ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት የምርምር ስትራጂዎች መካከል አንዱ እንዲሆን ከመደረጉ በተጨማሪ ፍልሰት እንደ አንድ ዋነኛ የማህበረሰብ አጀንዳ ተወሶዶ እንዲሰራበት መደረጉንም ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት የፕሮግራም ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ድርጅታቸው ለብሄራዊ ፍልሰት ምላሽ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከፍልሰት ምርምር የሚገኙ ግብዓቶች ደግሞ ፕሮግራሙ ይበልጥ በውጤታማነት እንዲፈጸም የሚያግዙ እቅዶችን ለማቀድ የሚረዱ በመሆናቸው ድርጅታቸው ምርምርን አጽዕኖት ሰጥቶ የሚደግፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት ባሉት የተለያዩ ችግሮች የተነሰ እየጨመሩ የመጡ የፍልሰት ተጋላጭነቶችንና ጉዳቶችን ለመቀንስ ቅንጅትና አስቸኳይ የጋራ ምላሾች የሚያስፈልጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር ብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብረሃም አያሌው ባለፉት ሦስት አመታት ፍልሰት ብሄራዊ የልማትና ደህንነት አጀንዳ ወደ መሆን የተሸጋገረ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህም በመሆኑ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በፍልሰት ላይ ያተኮረ የድህረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎች መክፈታቸውንና የተወሰኑት ደግሞ የፍልሰት ምርምር ማዕከላት ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀገራችን በዓለም አቀፍ፣ በአህጉርና በኢጋድ ሀገራት ደረጃ የተለያዩ የፍልሰት ስምምነቶችን ተቀብላ የህጎቿ አካል አድርጋ እየተገበረች መሆኗን ጠቅሰው ከጥቂት አመታት ወዲህ ለፍልሰት በተሰጠው ትኩረት ሀገራዊ የፍልሰት ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
በአውደ-ጥናቱ ላይ የተላያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ውጤታማነትና ለአውደ-ጥናቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
Nov 23, 2025 396
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ በሲንጋፖር አምባሳደር የተመራ የልዑካን ቡድንን ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሲንጋፖር አምባሳደርንና በሲንጋፖር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉዳይ ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን በማሻሻል ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለልኡካን ቡድኑ ገልፀዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በጀመረቻቸው አዳዲስ የልማት እቅዶች እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ቱሪዝም፣ ኒውክለር ሳይንስ እና በመሳሰሉት የትምህርት መስኮች ላይ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑን የመሩት አምባሳደር H.E Aselverjah በበኩላቸው ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ አጠናክራ በመቀጠል በቴክኖሎጂ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ፣ በሥርዓተ ትምህርትና ነጻ የትምህርት እድል በመስጠት ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
አያይዘውም በሲንጋፖር የትብብር ፕሮግራም የሰው ሃብት ልማት ፕሮጀክት እስከ አሁን 160 ሺህ በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በሲንጋፖር ዩኒቨርሲቲዎች መማራቸውና ከነዚህ ውስጥ 300 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት አብራርተዋል።
ይህንን ፕሮግራም በአሁኑ ሰዓት የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል የመስጠት ፍላጎት ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ክቡር ሚኒስትሩም የሚሰጠው የነጻ የትምህርት እድል በኢትዮጵያ በማይሰጡና አዲስ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ጠቃሚ በሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረጡ ተማሪዎችን በመላክ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሲንጋፖር አምባሳደርንና በሲንጋፖር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉዳይ ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን በማሻሻል ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለልኡካን ቡድኑ ገልፀዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በጀመረቻቸው አዳዲስ የልማት እቅዶች እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ቱሪዝም፣ ኒውክለር ሳይንስ እና በመሳሰሉት የትምህርት መስኮች ላይ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑን የመሩት አምባሳደር H.E Aselverjah በበኩላቸው ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ አጠናክራ በመቀጠል በቴክኖሎጂ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ፣ በሥርዓተ ትምህርትና ነጻ የትምህርት እድል በመስጠት ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
አያይዘውም በሲንጋፖር የትብብር ፕሮግራም የሰው ሃብት ልማት ፕሮጀክት እስከ አሁን 160 ሺህ በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በሲንጋፖር ዩኒቨርሲቲዎች መማራቸውና ከነዚህ ውስጥ 300 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት አብራርተዋል።
ይህንን ፕሮግራም በአሁኑ ሰዓት የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል የመስጠት ፍላጎት ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ክቡር ሚኒስትሩም የሚሰጠው የነጻ የትምህርት እድል በኢትዮጵያ በማይሰጡና አዲስ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ጠቃሚ በሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረጡ ተማሪዎችን በመላክ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
Nov 22, 2025 377
National News

የትምህርት ሚኒስትሩ የናይጄሪያ ቴክኒካል ድጋፍ በጎፈቃደኞች ድርጅት ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከናይጄሪያ ቴክኒክ ድጋፍ በጎፈቃደኞች ድርጅት ልዑክ ጋር በጽ/ቤታቸው ተወያይተዋል።

የሁለቱ አካላት ውይይት ናይጄሪያ ከዚህ ቀደም ለሀገራችን ስትሰጥ የነበረውና ተቋርጦ የቆየውን የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው ።
በዚሁ ጊዜ ናይጄሪያ ከኢትዮጵያጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን ያነሱት የልዑካን ቡድኑ መሪ ሀገራቸው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተዋል።
ነገር ግን ይህ የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱንና አሁን ላይ የናይጄሪያ መንግስት ይህንን በትምህርቱ ዘርፉ የሚያደርገውን የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል ፍላጎት ያለው በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማሰማራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለክቡር ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በበኩላቸው ይህ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረገው የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ሀገራችንን የበለጠ ተጠቃሚ እንድትሆን እንደሚያስችል እምነታቸውን መሆኑ ገልጸዋል።
‎በተለይም በሀገራችን ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉትን እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ኒውክለር ሳይንስ እና ለመሳሰሉት አዳዲስ የሙያ መስኮች የናይጄሪያ ተሞክሮ አስፈላጊ መሆኑን አንስተውላቸዋል።
‎በመሆኑም በነዚህ አዳዲስ የትምህርት መስኮች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ሙሁራንን ወደ አገራችን ቢመጡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በመላክ ልምድ እንዲወስዱ ቢደርግ ጠቃሚ እንደሚሆንም ለዑካን ቡድኑ ገልጸውላቸዋል።
ለዚህም ተግባራዊነት የልዑካን ቡድኑ መሪና የትምህርት ሚኒስቴር ቴክኒካል ቡድን ከላይ በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ዝርዝር ዝግጅት በቀጣይ እንዲደርግ ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ተስማምተዋል።
የሁለቱ አካላት ውይይት ናይጄሪያ ከዚህ ቀደም ለሀገራችን ስትሰጥ የነበረውና ተቋርጦ የቆየውን የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው ።

በዚሁ ጊዜ ናይጄሪያ ከኢትዮጵያጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን ያነሱት የልዑካን ቡድኑ መሪ ሀገራቸው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተዋል።

ነገር ግን ይህ የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱንና አሁን ላይ የናይጄሪያ መንግስት ይህንን በትምህርቱ ዘርፉ የሚያደርገውን የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል ፍላጎት ያለው በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማሰማራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለክቡር ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ በበኩላቸው ይህ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረገው የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ሀገራችንን የበለጠ ተጠቃሚ እንድትሆን እንደሚያስችል እምነታቸውን መሆኑ ገልጸዋል።

‎በተለይም በሀገራችን ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉትን እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ኒውክለር ሳይንስ እና ለመሳሰሉት አዳዲስ የሙያ መስኮች የናይጄሪያ ተሞክሮ አስፈላጊ መሆኑን አንስተውላቸዋል።
‎በመሆኑም በነዚህ አዳዲስ የትምህርት መስኮች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ሙሁራንን ወደ አገራችን ቢመጡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በመላክ ልምድ እንዲወስዱ ቢደርግ ጠቃሚ እንደሚሆንም ለዑካን ቡድኑ ገልጸውላቸዋል።

ለዚህም ተግባራዊነት የልዑካን ቡድኑ መሪና የትምህርት ሚኒስቴር ቴክኒካል ቡድን ከላይ በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ዝርዝር ዝግጅት በቀጣይ እንዲደርግ ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ተስማምተዋል።
Nov 21, 2025 607
Advertisement

ማስታወቂያ

ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ስራ አስፈጻሚ በ2 የተለያዩ ጉዳዮች ማለትም፤
1. በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣ ረቂቅ ደንብ ሊንክ = https://forms.gle/HisAZoyTpmo1ZFCA6
2. የተማሪዎች የሥነ-ምግባር መመሪያ (የመጀመሪያ ረቂቅ) ሊንክ =
በመሆኑም ሰነዶቹን በማንበብ አስተያየት እንድትሰጡ እየጠየቅን፤
 ለመጀመር ከእያንዳንዱ ረቂቅ መመሪያ ፊት ለፊት ያሉትን ሊንኮች መጫን፤
 በመቀጠል ማስፈንጠሪያ የሚለውን በመጫን ሰነዱን ማግኘት ትችላላችሁ፣
 ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ (submit) የሚለውን በመጫን መረጃውን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ስራ አስፈጻሚ በ2 የተለያዩ ጉዳዮች ማለትም፤
1. በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣ ረቂቅ ደንብ ሊንክ = https://forms.gle/HisAZoyTpmo1ZFCA6
2. የተማሪዎች የሥነ-ምግባር መመሪያ (የመጀመሪያ ረቂቅ) ሊንክ =
በመሆኑም ሰነዶቹን በማንበብ አስተያየት እንድትሰጡ እየጠየቅን፤
 ለመጀመር ከእያንዳንዱ ረቂቅ መመሪያ ፊት ለፊት ያሉትን ሊንኮች መጫን፤
 በመቀጠል ማስፈንጠሪያ የሚለውን በመጫን ሰነዱን ማግኘት ትችላላችሁ፣
 ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ (submit) የሚለውን በመጫን መረጃውን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
Nov 18, 2025 56
National News

ብዝሃነትና አካታችነትን በማረጋገጥ የዜጎችን እኩል ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተመላከተ ‎በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ Diversity & Inclusion በሚል ርዕስ ትምህርታዊ ውይይት ተካሂዷል።

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በከፍተኛ ትምህርት ዘርፉ ብዝሃነትና አካታችነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
‎ብዝሃነትና አካታችነትን በማረጋገጥ በዘርፉ ያሉ እድሎችን እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ቢሆንም ከሚጠበቀው አንጻር ብዙ መስራት እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል።
‎አካታችነትና ብዝሃነት የአመለካከት ጉዳይ መሆኑን የጠቆሙት ክቡር አቶ ኮራ ተግባራዊነቱን ለማረጋገጥና ለማስፋት ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
‎በከፍተኛ ትምህርት በውጤት ተኮር የትምህርት አሰጣጥና በብዝሓነትና አካታችነት ላይ ያተኮረውን ትምህርታዊ ገለጻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአካቶ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አለማየሁ ተክለ ማርያም ሰጥተዋል።
‎በከፍተኛ ትምህርት ብዝሃነት አካታችነትና ውጤት ተኮር የትምህርት አሰጣጥ ጥራቱን ለጠበቀ ትምህርት ወሳኝ መሆኑንም ፕሮፌሰር አለማየሁ ጨምረው ተናግረዋል።
በትምህርታዊ ገለጻው /Public Lecture / የተሳተፉ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች በእለቱ ያገኙትን እውቀትና መረጃ በተጨባጭ ለሚያከናውኑት ስራ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ጠቁመዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች/KPI/ ዕቅድ መሠረት በየሳምንቱ በተጋባዥ እንግዳ ትምህርታዊ የግንዛቤ ማስጨበጫና የእውቀት ሽግግር መድረክ እንደሚካሄድ ገልጸዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በከፍተኛ ትምህርት ዘርፉ ብዝሃነትና አካታችነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
‎ብዝሃነትና አካታችነትን በማረጋገጥ በዘርፉ ያሉ እድሎችን እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ቢሆንም ከሚጠበቀው አንጻር ብዙ መስራት እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል።
‎አካታችነትና ብዝሃነት የአመለካከት ጉዳይ መሆኑን የጠቆሙት ክቡር አቶ ኮራ ተግባራዊነቱን ለማረጋገጥና ለማስፋት ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
‎በከፍተኛ ትምህርት በውጤት ተኮር የትምህርት አሰጣጥና በብዝሓነትና አካታችነት ላይ ያተኮረውን ትምህርታዊ ገለጻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአካቶ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አለማየሁ ተክለ ማርያም ሰጥተዋል።
‎በከፍተኛ ትምህርት ብዝሃነት አካታችነትና ውጤት ተኮር የትምህርት አሰጣጥ ጥራቱን ለጠበቀ ትምህርት ወሳኝ መሆኑንም ፕሮፌሰር አለማየሁ ጨምረው ተናግረዋል።
በትምህርታዊ ገለጻው /Public Lecture / የተሳተፉ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች በእለቱ ያገኙትን እውቀትና መረጃ በተጨባጭ ለሚያከናውኑት ስራ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ጠቁመዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች/KPI/ ዕቅድ መሠረት በየሳምንቱ በተጋባዥ እንግዳ ትምህርታዊ የግንዛቤ ማስጨበጫና የእውቀት ሽግግር መድረክ እንደሚካሄድ ገልጸዋል።
Nov 11, 2025 35
National News

በግሪክ ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤት ተፈጥሮ የነበረውን ችግር ለመፍታት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

በግሪክ ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤት ተፈጥሮ የነበረውን ችግር ለመፍታት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በትምህርት ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ የግሪክ ኤምባሲ ተፈርሟል።
የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር እንዲሁም ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ፈርመውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በግሪክ ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት አመታት ከፍተኛ አለመግባባት ተፈጥሮ የነበረ መሆኑን አስታውሰው ይህ የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ችግሩን ሙሉ በሙሉ በመፍታት ለዜጎች ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለመስጠት ያስችላል ብለዋል።
አክለውም ኢትዮጵያና ግሪክ ለረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተው ከት/ቤቱ ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን የቆየ ችግር ለመፍታትና የትምህርት ቤቱን ሌጋሲ ለማስቀጠል በትምህርት ሚኒስቴር፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እንዲሁም እንደ መንግስት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል።
ይህ ትምህርት ቤት የግሪክ መንግስት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ለጥሩ ዓላማ ያቋቋመውና ለረጅም ጊዜ ሲሰራ የቆየ ትምህርት ቤት መሆኑን ገልጸው በመሃል መስመሩን ስቶ ነበር ያሉት ሚኒስትሩ አሁን የት/ቤቱን ስምና ታሪክ ባስጠበቀ መልኩ እንደገና ለማስቀጠል መንግስት ባቋቋመው ቦርድ የሚመራ የህዝብ ትምህርት ቤት እንዲሆን በጋራ ከስምምነት መደረሱን አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር አንቶኒዬስ እዝጉሮፑሎስ በበኩላቸው በሁለቱ ሀገራት መካከል በባህል፣ በትምህርትና በሌሎች ዘርፎች ጠንካራ ግንኙነት እንደነበር ጠቅሰው በትምህርት ቤቱ በኩል ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት ለመፍታት ሰፊ ጊዜ የወሰደ ስኬታማ ውይይት ከተደረገ በኋላ ለዚህ ስምምነት መደረሱን ተናግረዋል።
ስምምነቱ የግሪክ ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤትን መልሶ በመቋቋም ትምህርት ቤቱ ፍትሃዊ፣ ጥራት ያለውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች ያለምንም ልዩነት የሚማሩበት የትምህርት ተቋም እንዲሆን በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ተቀራርበው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ከዚህ ስምምነት እንዲደረስና የነበሩ አለመግባባቶች እንዲፈቱ የትምህርት ሚኒስትሩ ላደረጉት ከፍተኛ ጥረትም አምባሳደሩ አመስግነዋል።
ይህ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት የቆየ የትምህርት ዘርፍ ትብብር በማጠናከር ረገድ ሚናው የጎላ እንደሚሆን በመድረኩ ተገልጿል።
በግሪክ ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤት ተፈጥሮ የነበረውን ችግር ለመፍታት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በትምህርት ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ የግሪክ ኤምባሲ ተፈርሟል።
የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር እንዲሁም ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ፈርመውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በግሪክ ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት አመታት ከፍተኛ አለመግባባት ተፈጥሮ የነበረ መሆኑን አስታውሰው ይህ የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ችግሩን ሙሉ በሙሉ በመፍታት ለዜጎች ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለመስጠት ያስችላል ብለዋል።
አክለውም ኢትዮጵያና ግሪክ ለረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተው ከት/ቤቱ ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን የቆየ ችግር ለመፍታትና የትምህርት ቤቱን ሌጋሲ ለማስቀጠል በትምህርት ሚኒስቴር፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እንዲሁም እንደ መንግስት ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል።
ይህ ትምህርት ቤት የግሪክ መንግስት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር ለጥሩ ዓላማ ያቋቋመውና ለረጅም ጊዜ ሲሰራ የቆየ ትምህርት ቤት መሆኑን ገልጸው በመሃል መስመሩን ስቶ ነበር ያሉት ሚኒስትሩ አሁን የት/ቤቱን ስምና ታሪክ ባስጠበቀ መልኩ እንደገና ለማስቀጠል መንግስት ባቋቋመው ቦርድ የሚመራ የህዝብ ትምህርት ቤት እንዲሆን በጋራ ከስምምነት መደረሱን አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር አንቶኒዬስ እዝጉሮፑሎስ በበኩላቸው በሁለቱ ሀገራት መካከል በባህል፣ በትምህርትና በሌሎች ዘርፎች ጠንካራ ግንኙነት እንደነበር ጠቅሰው በትምህርት ቤቱ በኩል ተፈጥሮ የነበረውን አለመግባባት ለመፍታት ሰፊ ጊዜ የወሰደ ስኬታማ ውይይት ከተደረገ በኋላ ለዚህ ስምምነት መደረሱን ተናግረዋል።
ስምምነቱ የግሪክ ኮሙዩኒቲ ትምህርት ቤትን መልሶ በመቋቋም ትምህርት ቤቱ ፍትሃዊ፣ ጥራት ያለውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎች ያለምንም ልዩነት የሚማሩበት የትምህርት ተቋም እንዲሆን በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ተቀራርበው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ከዚህ ስምምነት እንዲደረስና የነበሩ አለመግባባቶች እንዲፈቱ የትምህርት ሚኒስትሩ ላደረጉት ከፍተኛ ጥረትም አምባሳደሩ አመስግነዋል።
ይህ ስምምነት የሁለቱን ሀገራት የቆየ የትምህርት ዘርፍ ትብብር በማጠናከር ረገድ ሚናው የጎላ እንደሚሆን በመድረኩ ተገልጿል።
Nov 11, 2025 36
National News

የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር ጠንካራ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትና ለሞራል ግንባታ መሰረት የሆነ ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረ አድርጎ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ፤ ‎34ኛው የትምህርት ጉባዔ በኦሮሚያ ብ/ክ/መ በአዳማ ከተማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጉባኤውን ሲከፍቱ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር ጠንካራ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትና ለየሞራል ግንባታ መሰረት የሆነ ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረ አድርጎ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
‎የተሻለ ዜጋ ለመፍጠር ጥራትና ፍትሃዊነትን የተረጋገጥ ትምህርት ከማቅረብ ባሻገር በጠንካራ ሞራል መሠረት ላይ የቆመ ዜጋ መፍጠር እንደሚገባም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጨምረው አስገንዝበዋል።
‎የተማሩ ብቃትና ችሎታ ያላቸውን ዜጎች ለማፍራት ከመጀመሪያ ደረጃ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ጥልቀት ያለው እውቀት መስጠት እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
‎በትምህርቱ ዘርፍ እየተካሄዱ ያሉ የሪፎርም ስራዎች በተለይም የሞራል ልዕል ያለው ዜጋ ለመገንባት እየተካሄደ ባለው ስራ በማህበረሰቡ ዘንድ የተሻ መረዳት መፈጠሩንም ጠቁመዋል።
‎የጉባዔው አዘጋጅ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት አመታት በትምህርት ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች ትልቅ እድገት መመዝገቡን ተናግረዋል።
‎በዘርፉ ከትምህርት የራቁ ዜጎችን ወደ ትምህርት ገበታ ከማምጣት ፣የመማሪያ ቁሳቁስ ከማሟላት፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ አንጻር አሁንም ተግዳሮቶች መኖራቸውን ዶክተር ቶላ አስረድተዋል።
‎34ኛው የትምህርት ጉባዔ አገራችን ማንሰራራት በጀመረችበት ዘመን የሚካሄድ መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም የትምህርት ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጉባኤውን ሲከፍቱ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር ጠንካራ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትና ለየሞራል ግንባታ መሰረት የሆነ ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረ አድርጎ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
‎የተሻለ ዜጋ ለመፍጠር ጥራትና ፍትሃዊነትን የተረጋገጥ ትምህርት ከማቅረብ ባሻገር በጠንካራ ሞራል መሠረት ላይ የቆመ ዜጋ መፍጠር እንደሚገባም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጨምረው አስገንዝበዋል።
‎የተማሩ ብቃትና ችሎታ ያላቸውን ዜጎች ለማፍራት ከመጀመሪያ ደረጃ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ጥልቀት ያለው እውቀት መስጠት እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
‎በትምህርቱ ዘርፍ እየተካሄዱ ያሉ የሪፎርም ስራዎች በተለይም የሞራል ልዕል ያለው ዜጋ ለመገንባት እየተካሄደ ባለው ስራ በማህበረሰቡ ዘንድ የተሻ መረዳት መፈጠሩንም ጠቁመዋል።
‎የጉባዔው አዘጋጅ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት አመታት በትምህርት ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች ትልቅ እድገት መመዝገቡን ተናግረዋል።
‎በዘርፉ ከትምህርት የራቁ ዜጎችን ወደ ትምህርት ገበታ ከማምጣት ፣የመማሪያ ቁሳቁስ ከማሟላት፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ አንጻር አሁንም ተግዳሮቶች መኖራቸውን ዶክተር ቶላ አስረድተዋል።
‎34ኛው የትምህርት ጉባዔ አገራችን ማንሰራራት በጀመረችበት ዘመን የሚካሄድ መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም የትምህርት ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል።
Nov 11, 2025 654
Recent News
Follow Us