ዜና

የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ ከደቡብ አፍሪካ የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይትም University of South Africa (UNISA) በኢትዮጵያ እንዴት በትብብር መስራት እንደሚችል ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የUnisa’s Principal and Vice-Chancellor Prof Puleng LenkaBula ፤ UNISA ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ከ2006 ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ መስክ በርካታ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ሲያስመርቅ መቆየቱን ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከፍተኛ ችግር የነበረበትና በከፍተኛ ትምህርት ዜጎች ዲግሪ በገንዘብ የሚገዙበት ጭምር የነበረ በመሆኑ፤
ይህንን ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የትምህርት ጥራትን ሊያረጋግጡ እንዲሁም ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ መሆኑና በዚህም ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ዓለም በፈጣን እድገት ላይ ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ በጣም ውስብስብ እየሆነች መጥታለች ያሉት ሚኒስትሩ UNISA ከ20 ዓመት በፊት በጀመረው ስምምነትና ፕሮግራም መሰረት አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፍላጎትና የኢኮኖሚ እድገት ሊቀጥል የማይችል በመሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያስችል መልኩ መታየት እንዳለበት አስገንዝበው በአፍሪካ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮች ይህንን መሰረት ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ሥራዎችም ሀገራችን ለያዘቻቸው የልማት እቅዶች መሳካት የሚያስፈልግ የሰው ሃይል ልማትን በሚያግዙ የትምህርት መስኮች እንደ ማዕድን፣ ፔትሮ ኬሚካል፣ አግሮ ኢንደስትሪ የመሳሰሉት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን ይገባቸዋልም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው UNISA በሀገራችን ላለፉት 20 ዓመታት ሲሰራ መቆየቱ ቢታወቅም፣ በቀጣይ የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲስ ውይይት ማድረግ ይቻላል ብለዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየትኞቹ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት እንደሚቻል እንዲለዩና ለቀጣይ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲቀርቡ ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የUNISA ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አመራሮች ተግኝተዋል።
በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የUnisa’s Principal and Vice-Chancellor Prof Puleng LenkaBula ፤ UNISA ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ከ2006 ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ መስክ በርካታ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ሲያስመርቅ መቆየቱን ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከፍተኛ ችግር የነበረበትና በከፍተኛ ትምህርት ዜጎች ዲግሪ በገንዘብ የሚገዙበት ጭምር የነበረ በመሆኑ፤
ይህንን ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የትምህርት ጥራትን ሊያረጋግጡ እንዲሁም ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ መሆኑና በዚህም ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ዓለም በፈጣን እድገት ላይ ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ በጣም ውስብስብ እየሆነች መጥታለች ያሉት ሚኒስትሩ UNISA ከ20 ዓመት በፊት በጀመረው ስምምነትና ፕሮግራም መሰረት አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፍላጎትና የኢኮኖሚ እድገት ሊቀጥል የማይችል በመሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያስችል መልኩ መታየት እንዳለበት አስገንዝበው በአፍሪካ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮች ይህንን መሰረት ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ሥራዎችም ሀገራችን ለያዘቻቸው የልማት እቅዶች መሳካት የሚያስፈልግ የሰው ሃይል ልማትን በሚያግዙ የትምህርት መስኮች እንደ ማዕድን፣ ፔትሮ ኬሚካል፣ አግሮ ኢንደስትሪ የመሳሰሉት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን ይገባቸዋልም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው UNISA በሀገራችን ላለፉት 20 ዓመታት ሲሰራ መቆየቱ ቢታወቅም፣ በቀጣይ የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲስ ውይይት ማድረግ ይቻላል ብለዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየትኞቹ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት እንደሚቻል እንዲለዩና ለቀጣይ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲቀርቡ ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የUNISA ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አመራሮች ተግኝተዋል።
Nov 29, 2025 25
የሀገር ውስጥ ዜና

እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስ በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም እቀፍ ህጻናት አድን ድርጅት ጋር በመተባበር” በኢትዮጵያ የፍልሰት ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሲቪክ ማህባራት፣መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ-ጥናት ተካሂዷል፡፡
በአውደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስቴር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስም ሆነ በሚገባ ለማስተዳደር በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻና አጋር አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
አውደ-ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች የጋራ ትብብርና ቅንጅት በሚሰሩ ምርምሮች የሚለዩ የህግ ማዕቀፎችና የአተገባበር ክፍተቶች አግባብነት ባላቸው ተቋማት ተወስደው ለአስፈጻሚዎች ውሳኔና ለፋጻሚዎች ትግበራ ማሻሻያነት የሚውሉበት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮፌሰር ክንደያ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለፍልሰት በተሰጠው ሀገራዊ ትኩረት የፍልሰት ምርምር ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት የምርምር ስትራጂዎች መካከል አንዱ እንዲሆን ከመደረጉ በተጨማሪ ፍልሰት እንደ አንድ ዋነኛ የማህበረሰብ አጀንዳ ተወሶዶ እንዲሰራበት መደረጉንም ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት የፕሮግራም ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ድርጅታቸው ለብሄራዊ ፍልሰት ምላሽ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከፍልሰት ምርምር የሚገኙ ግብዓቶች ደግሞ ፕሮግራሙ ይበልጥ በውጤታማነት እንዲፈጸም የሚያግዙ እቅዶችን ለማቀድ የሚረዱ በመሆናቸው ድርጅታቸው ምርምርን አጽዕኖት ሰጥቶ የሚደግፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት ባሉት የተለያዩ ችግሮች የተነሰ እየጨመሩ የመጡ የፍልሰት ተጋላጭነቶችንና ጉዳቶችን ለመቀንስ ቅንጅትና አስቸኳይ የጋራ ምላሾች የሚያስፈልጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር ብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብረሃም አያሌው ባለፉት ሦስት አመታት ፍልሰት ብሄራዊ የልማትና ደህንነት አጀንዳ ወደ መሆን የተሸጋገረ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህም በመሆኑ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በፍልሰት ላይ ያተኮረ የድህረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎች መክፈታቸውንና የተወሰኑት ደግሞ የፍልሰት ምርምር ማዕከላት ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀገራችን በዓለም አቀፍ፣ በአህጉርና በኢጋድ ሀገራት ደረጃ የተለያዩ የፍልሰት ስምምነቶችን ተቀብላ የህጎቿ አካል አድርጋ እየተገበረች መሆኗን ጠቅሰው ከጥቂት አመታት ወዲህ ለፍልሰት በተሰጠው ትኩረት ሀገራዊ የፍልሰት ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
በአውደ-ጥናቱ ላይ የተላያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ውጤታማነትና ለአውደ-ጥናቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም እቀፍ ህጻናት አድን ድርጅት ጋር በመተባበር” በኢትዮጵያ የፍልሰት ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሲቪክ ማህባራት፣መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ-ጥናት ተካሂዷል፡፡
በአውደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስቴር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስም ሆነ በሚገባ ለማስተዳደር በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻና አጋር አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
አውደ-ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች የጋራ ትብብርና ቅንጅት በሚሰሩ ምርምሮች የሚለዩ የህግ ማዕቀፎችና የአተገባበር ክፍተቶች አግባብነት ባላቸው ተቋማት ተወስደው ለአስፈጻሚዎች ውሳኔና ለፋጻሚዎች ትግበራ ማሻሻያነት የሚውሉበት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮፌሰር ክንደያ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለፍልሰት በተሰጠው ሀገራዊ ትኩረት የፍልሰት ምርምር ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት የምርምር ስትራጂዎች መካከል አንዱ እንዲሆን ከመደረጉ በተጨማሪ ፍልሰት እንደ አንድ ዋነኛ የማህበረሰብ አጀንዳ ተወሶዶ እንዲሰራበት መደረጉንም ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት የፕሮግራም ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ድርጅታቸው ለብሄራዊ ፍልሰት ምላሽ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከፍልሰት ምርምር የሚገኙ ግብዓቶች ደግሞ ፕሮግራሙ ይበልጥ በውጤታማነት እንዲፈጸም የሚያግዙ እቅዶችን ለማቀድ የሚረዱ በመሆናቸው ድርጅታቸው ምርምርን አጽዕኖት ሰጥቶ የሚደግፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት ባሉት የተለያዩ ችግሮች የተነሰ እየጨመሩ የመጡ የፍልሰት ተጋላጭነቶችንና ጉዳቶችን ለመቀንስ ቅንጅትና አስቸኳይ የጋራ ምላሾች የሚያስፈልጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር ብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብረሃም አያሌው ባለፉት ሦስት አመታት ፍልሰት ብሄራዊ የልማትና ደህንነት አጀንዳ ወደ መሆን የተሸጋገረ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህም በመሆኑ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በፍልሰት ላይ ያተኮረ የድህረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎች መክፈታቸውንና የተወሰኑት ደግሞ የፍልሰት ምርምር ማዕከላት ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀገራችን በዓለም አቀፍ፣ በአህጉርና በኢጋድ ሀገራት ደረጃ የተለያዩ የፍልሰት ስምምነቶችን ተቀብላ የህጎቿ አካል አድርጋ እየተገበረች መሆኗን ጠቅሰው ከጥቂት አመታት ወዲህ ለፍልሰት በተሰጠው ትኩረት ሀገራዊ የፍልሰት ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
በአውደ-ጥናቱ ላይ የተላያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ውጤታማነትና ለአውደ-ጥናቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
Nov 23, 2025 23
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ በሲንጋፖር አምባሳደር የተመራ የልዑካን ቡድንን ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሲንጋፖር አምባሳደርንና በሲንጋፖር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉዳይ ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን በማሻሻል ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለልኡካን ቡድኑ ገልፀዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በጀመረቻቸው አዳዲስ የልማት እቅዶች እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ቱሪዝም፣ ኒውክለር ሳይንስ እና በመሳሰሉት የትምህርት መስኮች ላይ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑን የመሩት አምባሳደር H.E Aselverjah በበኩላቸው ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ አጠናክራ በመቀጠል በቴክኖሎጂ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ፣ በሥርዓተ ትምህርትና ነጻ የትምህርት እድል በመስጠት ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
አያይዘውም በሲንጋፖር የትብብር ፕሮግራም የሰው ሃብት ልማት ፕሮጀክት እስከ አሁን 160 ሺህ በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በሲንጋፖር ዩኒቨርሲቲዎች መማራቸውና ከነዚህ ውስጥ 300 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት አብራርተዋል።
ይህንን ፕሮግራም በአሁኑ ሰዓት የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል የመስጠት ፍላጎት ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ክቡር ሚኒስትሩም የሚሰጠው የነጻ የትምህርት እድል በኢትዮጵያ በማይሰጡና አዲስ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ጠቃሚ በሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረጡ ተማሪዎችን በመላክ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሲንጋፖር አምባሳደርንና በሲንጋፖር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉዳይ ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን በማሻሻል ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለልኡካን ቡድኑ ገልፀዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በጀመረቻቸው አዳዲስ የልማት እቅዶች እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ቱሪዝም፣ ኒውክለር ሳይንስ እና በመሳሰሉት የትምህርት መስኮች ላይ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑን የመሩት አምባሳደር H.E Aselverjah በበኩላቸው ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ አጠናክራ በመቀጠል በቴክኖሎጂ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ፣ በሥርዓተ ትምህርትና ነጻ የትምህርት እድል በመስጠት ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
አያይዘውም በሲንጋፖር የትብብር ፕሮግራም የሰው ሃብት ልማት ፕሮጀክት እስከ አሁን 160 ሺህ በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በሲንጋፖር ዩኒቨርሲቲዎች መማራቸውና ከነዚህ ውስጥ 300 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት አብራርተዋል።
ይህንን ፕሮግራም በአሁኑ ሰዓት የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል የመስጠት ፍላጎት ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ክቡር ሚኒስትሩም የሚሰጠው የነጻ የትምህርት እድል በኢትዮጵያ በማይሰጡና አዲስ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ጠቃሚ በሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረጡ ተማሪዎችን በመላክ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
Nov 22, 2025 17
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ የናይጄሪያ ቴክኒካል ድጋፍ በጎፈቃደኞች ድርጅት ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከናይጄሪያ ቴክኒክ ድጋፍ በጎፈቃደኞች ድርጅት ልዑክ ጋር በጽ/ቤታቸው ተወያይተዋል።

የሁለቱ አካላት ውይይት ናይጄሪያ ከዚህ ቀደም ለሀገራችን ስትሰጥ የነበረውና ተቋርጦ የቆየውን የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው ።

በዚሁ ጊዜ ናይጄሪያ ከኢትዮጵያጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን ያነሱት የልዑካን ቡድኑ መሪ ሀገራቸው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተዋል።

ነገር ግን ይህ የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱንና አሁን ላይ የናይጄሪያ መንግስት ይህንን በትምህርቱ ዘርፉ የሚያደርገውን የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል ፍላጎት ያለው በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማሰማራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለክቡር ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ በበኩላቸው ይህ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረገው የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ሀገራችንን የበለጠ ተጠቃሚ እንድትሆን እንደሚያስችል እምነታቸውን መሆኑ ገልጸዋል።

‎በተለይም በሀገራችን ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉትን እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ኒውክለር ሳይንስ እና ለመሳሰሉት አዳዲስ የሙያ መስኮች የናይጄሪያ ተሞክሮ አስፈላጊ መሆኑን አንስተውላቸዋል።
‎በመሆኑም በነዚህ አዳዲስ የትምህርት መስኮች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ሙሁራንን ወደ አገራችን ቢመጡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በመላክ ልምድ እንዲወስዱ ቢደርግ ጠቃሚ እንደሚሆንም ለዑካን ቡድኑ ገልጸውላቸዋል።

ለዚህም ተግባራዊነት የልዑካን ቡድኑ መሪና የትምህርት ሚኒስቴር ቴክኒካል ቡድን ከላይ በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ዝርዝር ዝግጅት በቀጣይ እንዲደርግ ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ተስማምተዋል።
የሁለቱ አካላት ውይይት ናይጄሪያ ከዚህ ቀደም ለሀገራችን ስትሰጥ የነበረውና ተቋርጦ የቆየውን የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው ።

በዚሁ ጊዜ ናይጄሪያ ከኢትዮጵያጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን ያነሱት የልዑካን ቡድኑ መሪ ሀገራቸው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተዋል።

ነገር ግን ይህ የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱንና አሁን ላይ የናይጄሪያ መንግስት ይህንን በትምህርቱ ዘርፉ የሚያደርገውን የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል ፍላጎት ያለው በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማሰማራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለክቡር ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ በበኩላቸው ይህ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረገው የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ሀገራችንን የበለጠ ተጠቃሚ እንድትሆን እንደሚያስችል እምነታቸውን መሆኑ ገልጸዋል።

‎በተለይም በሀገራችን ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉትን እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ኒውክለር ሳይንስ እና ለመሳሰሉት አዳዲስ የሙያ መስኮች የናይጄሪያ ተሞክሮ አስፈላጊ መሆኑን አንስተውላቸዋል።
‎በመሆኑም በነዚህ አዳዲስ የትምህርት መስኮች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ሙሁራንን ወደ አገራችን ቢመጡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በመላክ ልምድ እንዲወስዱ ቢደርግ ጠቃሚ እንደሚሆንም ለዑካን ቡድኑ ገልጸውላቸዋል።

ለዚህም ተግባራዊነት የልዑካን ቡድኑ መሪና የትምህርት ሚኒስቴር ቴክኒካል ቡድን ከላይ በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ዝርዝር ዝግጅት በቀጣይ እንዲደርግ ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ተስማምተዋል።
Nov 21, 2025 336
የሀገር ውስጥ ዜና

የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር ጠንካራ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትና ለሞራል ግንባታ መሰረት የሆነ ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረ አድርጎ መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ፤ ‎34ኛው የትምህርት ጉባዔ በኦሮሚያ ብ/ክ/መ በአዳማ ከተማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጉባኤውን ሲከፍቱ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር ጠንካራ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትና ለየሞራል ግንባታ መሰረት የሆነ ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረ አድርጎ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
‎የተሻለ ዜጋ ለመፍጠር ጥራትና ፍትሃዊነትን የተረጋገጥ ትምህርት ከማቅረብ ባሻገር በጠንካራ ሞራል መሠረት ላይ የቆመ ዜጋ መፍጠር እንደሚገባም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጨምረው አስገንዝበዋል።
‎የተማሩ ብቃትና ችሎታ ያላቸውን ዜጎች ለማፍራት ከመጀመሪያ ደረጃ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ጥልቀት ያለው እውቀት መስጠት እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
‎በትምህርቱ ዘርፍ እየተካሄዱ ያሉ የሪፎርም ስራዎች በተለይም የሞራል ልዕል ያለው ዜጋ ለመገንባት እየተካሄደ ባለው ስራ በማህበረሰቡ ዘንድ የተሻ መረዳት መፈጠሩንም ጠቁመዋል።
‎የጉባዔው አዘጋጅ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት አመታት በትምህርት ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች ትልቅ እድገት መመዝገቡን ተናግረዋል።
‎በዘርፉ ከትምህርት የራቁ ዜጎችን ወደ ትምህርት ገበታ ከማምጣት ፣የመማሪያ ቁሳቁስ ከማሟላት፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ አንጻር አሁንም ተግዳሮቶች መኖራቸውን ዶክተር ቶላ አስረድተዋል።
‎34ኛው የትምህርት ጉባዔ አገራችን ማንሰራራት በጀመረችበት ዘመን የሚካሄድ መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም የትምህርት ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጉባኤውን ሲከፍቱ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር ጠንካራ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትና ለየሞራል ግንባታ መሰረት የሆነ ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረ አድርጎ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
‎የተሻለ ዜጋ ለመፍጠር ጥራትና ፍትሃዊነትን የተረጋገጥ ትምህርት ከማቅረብ ባሻገር በጠንካራ ሞራል መሠረት ላይ የቆመ ዜጋ መፍጠር እንደሚገባም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጨምረው አስገንዝበዋል።
‎የተማሩ ብቃትና ችሎታ ያላቸውን ዜጎች ለማፍራት ከመጀመሪያ ደረጃ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ጥልቀት ያለው እውቀት መስጠት እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
‎በትምህርቱ ዘርፍ እየተካሄዱ ያሉ የሪፎርም ስራዎች በተለይም የሞራል ልዕል ያለው ዜጋ ለመገንባት እየተካሄደ ባለው ስራ በማህበረሰቡ ዘንድ የተሻ መረዳት መፈጠሩንም ጠቁመዋል።
‎የጉባዔው አዘጋጅ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፉት አመታት በትምህርት ዘርፍ በተከናወኑ ሥራዎች ትልቅ እድገት መመዝገቡን ተናግረዋል።
‎በዘርፉ ከትምህርት የራቁ ዜጎችን ወደ ትምህርት ገበታ ከማምጣት ፣የመማሪያ ቁሳቁስ ከማሟላት፣ በቴክኖሎጂና ፈጠራ አንጻር አሁንም ተግዳሮቶች መኖራቸውን ዶክተር ቶላ አስረድተዋል።
‎34ኛው የትምህርት ጉባዔ አገራችን ማንሰራራት በጀመረችበት ዘመን የሚካሄድ መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም የትምህርት ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል።
Nov 11, 2025 466
የሀገር ውስጥ ዜና

በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ስራዎች ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ሀገርን ለማሻገር ቁልፍ ሚና እንዳለው ተገለጸ። አስረኛው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይና ውድድር በይፋ ተከፍቷል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከሌሎች ተባባሪ ተቋማት ጋር በመሆን የሚያዘጋጀው አመታዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይና ውድድር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል።
በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ልዩ ዝንባሌና ተሰጥኦ ያላቸውን ተማሪዎችና መምህራን የሚያገናኘውን አመታዊ አውደ ርዕይና ውድድር የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በይፋ ከፍተውታል።
ሚንስትር ዴኤታዋ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ሀገርን ለማሻገር በሳይንስና ቴክኖሎጂ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ቁልፍ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲና የሌሎች ተባባሪ ተቋማት ስራ ሀላፊዎች ቁልፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከሌሎች ተባባሪ ተቋማት ጋር በመሆን የሚያዘጋጀው አመታዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይና ውድድር በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል።
በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ልዩ ዝንባሌና ተሰጥኦ ያላቸውን ተማሪዎችና መምህራን የሚያገናኘውን አመታዊ አውደ ርዕይና ውድድር የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በይፋ ከፍተውታል።
ሚንስትር ዴኤታዋ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ሀገርን ለማሻገር በሳይንስና ቴክኖሎጂ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ቁልፍ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲና የሌሎች ተባባሪ ተቋማት ስራ ሀላፊዎች ቁልፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
Nov 11, 2025 493
የሀገር ውስጥ ዜና

34ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባዔ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተጀመረ፤

'ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም'' በሚል መሪ ቃል በተጀመረው ጉባዔ የ2017 የትምህርት ልማት ዘርፍ አፈጻጸም ይገመገማል።
‎ጉባዌው በ2018 የትምህርት ዘመን እቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ለተሻለ አፈጻጸም የሚያግዙ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
‎በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገር አቀፍ ጉባዔ የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
‎በተጨማሪም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ፣የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፣የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶችና አጋሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
'ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም'' በሚል መሪ ቃል በተጀመረው ጉባዔ የ2017 የትምህርት ልማት ዘርፍ አፈጻጸም ይገመገማል።
‎ጉባዌው በ2018 የትምህርት ዘመን እቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ለተሻለ አፈጻጸም የሚያግዙ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
‎በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገር አቀፍ ጉባዔ የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
‎በተጨማሪም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ፣የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፣የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶችና አጋሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
Nov 11, 2025 468
የሀገር ውስጥ ዜና

ትውልድን የመገንባት መንገዳችን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ስለሆነ ዘርፉን የሚያሻግሩ አማራጮችን ማስፋት እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ አሳሰቡ፤

ትውልድን የመገንባት መንገዳችን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ስለሆነ ዘርፉን የሚያሻግሩ አማራጮችን ማስፋት እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ አሳስበዋል።
በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የለውጥ ተግባራት ተነድፈው እየተተገበሩ መሆኑት የገለጹት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ባለፈው የትምህርት ዘመን ጸድቆ ወደትግብራ የገባውን የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ በሚገባ መተግበር ይገባል ብለዋል።
አያይዘውም ለተማሪዎች ውጤታማነት የትምህርት ቤት ምገባ፣ የመምህራንና የት/ቤት አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና በትኩረት እየተሰሩ መሆኑን አንስተው በዚህ ዓመትም ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሰገንዝበዋል።
በተጨማሪም የመምህራን የጥቅማጥቅምና መሠል ጥያቄዎችን ለመመለስ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች የእቅዳቸው አካል አርጎ ከመስራት ባለፈ በአካባቢ ያለን ሀብት አሟጦ በመጠቀም ለሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መልስ መስጠት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ለተቀመጡ ቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም የክልልና የከተማ መስተዳድር ት/ቢሮዎች ተጠያቂነትን በማረጋገጥ በሀላፊነት መንፈስ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ትውልድን የመገንባት መንገዳችን ረጅም ጊዜ የሚጠይቅ ስለሆነ ዘርፉን የሚያሻግሩ አማራጮችን ማስፋት እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ አሳስበዋል።
በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የለውጥ ተግባራት ተነድፈው እየተተገበሩ መሆኑት የገለጹት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ባለፈው የትምህርት ዘመን ጸድቆ ወደትግብራ የገባውን የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ በሚገባ መተግበር ይገባል ብለዋል።
አያይዘውም ለተማሪዎች ውጤታማነት የትምህርት ቤት ምገባ፣ የመምህራንና የት/ቤት አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና በትኩረት እየተሰሩ መሆኑን አንስተው በዚህ ዓመትም ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሰገንዝበዋል።
በተጨማሪም የመምህራን የጥቅማጥቅምና መሠል ጥያቄዎችን ለመመለስ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች የእቅዳቸው አካል አርጎ ከመስራት ባለፈ በአካባቢ ያለን ሀብት አሟጦ በመጠቀም ለሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መልስ መስጠት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ለተቀመጡ ቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም የክልልና የከተማ መስተዳድር ት/ቢሮዎች ተጠያቂነትን በማረጋገጥ በሀላፊነት መንፈስ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
Nov 11, 2025 433
የሀገር ውስጥ ዜና

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ለታቀዱ የሪፎርም ተግባራት መሳካት ሁሉም አካላት የሚጠበቅባቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ፤

የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በ34ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ እንደገለጹት በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ለታቀዱ የሪፎርም ተግባራት መሳካት ሁሉም አካላት የሚጠበቅባቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
‎በዚህም የኢንዱስትሪዎችና የትምህርት ተቋማት ትብብር መሥራት ሁለቱንም አካላት የሚጠቅም ተግባር መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎አያይዘውም የዩኒቨርስቲዎች በመማር ማስተማር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ስራ ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ገልጸው ከየዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ምገባ ጋር በተያያዘ ኃላፊነት ወስዶ የሚከታተል ተቋም ለማቋቋም እቅድ መኖሩንም ተናግረዋል።
‎ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም የዩኒቨርስቲዎች የትኩረት መስክ ልየታ በሂደት እየተሳካ የሚሄድ መሆኑን ገልጸው በዚህ ሂደት የሚፈጠሩ የመምህራንን እጥረትና ከምችት ለማሰተካከል አዘዋውሮ የማሰራት አቅጣጫ መኖሩንም ጠቁመዋል።
‎የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በትኩረት ለመደገፍ የተለየ የህግ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጨምረው አብራርተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በ34ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ እንደገለጹት በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ለታቀዱ የሪፎርም ተግባራት መሳካት ሁሉም አካላት የሚጠበቅባቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
‎በዚህም የኢንዱስትሪዎችና የትምህርት ተቋማት ትብብር መሥራት ሁለቱንም አካላት የሚጠቅም ተግባር መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎አያይዘውም የዩኒቨርስቲዎች በመማር ማስተማር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ስራ ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ገልጸው ከየዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ምገባ ጋር በተያያዘ ኃላፊነት ወስዶ የሚከታተል ተቋም ለማቋቋም እቅድ መኖሩንም ተናግረዋል።
‎ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም የዩኒቨርስቲዎች የትኩረት መስክ ልየታ በሂደት እየተሳካ የሚሄድ መሆኑን ገልጸው በዚህ ሂደት የሚፈጠሩ የመምህራንን እጥረትና ከምችት ለማሰተካከል አዘዋውሮ የማሰራት አቅጣጫ መኖሩንም ጠቁመዋል።
‎የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በትኩረት ለመደገፍ የተለየ የህግ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጨምረው አብራርተዋል።
Nov 11, 2025 376
የሀገር ውስጥ ዜና

የት/ቤት ምገባን በማጠናከር የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ማሳደግ ይገባል፤ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

በ34ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕ/ር ክንደያ ገ/ህይዎት የት/ቤት ምገባን በማጠናከር የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
ፕ/ር ክንደያ አክለውም የትምህርት ማህበረሰቡ በ “ትምህርት ለትውልድ“ያሳየውን የላቀ ተሳትፎ በአዳሪ እና በሞዴል ት/ቤቶች ግንባታም አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
የሪፎርም ስራዎቻችንና አበይት ስራዎቻችንን በሚገባ ለይተን በዚህ የትምህርት ዘመን ውጤት ሊያመጡ በሚችል መልኩ መተግባር እንደሚገባም ተናገረዋል።
በ34ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕ/ር ክንደያ ገ/ህይዎት የት/ቤት ምገባን በማጠናከር የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
ፕ/ር ክንደያ አክለውም የትምህርት ማህበረሰቡ በ “ትምህርት ለትውልድ“ያሳየውን የላቀ ተሳትፎ በአዳሪ እና በሞዴል ት/ቤቶች ግንባታም አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
የሪፎርም ስራዎቻችንና አበይት ስራዎቻችንን በሚገባ ለይተን በዚህ የትምህርት ዘመን ውጤት ሊያመጡ በሚችል መልኩ መተግባር እንደሚገባም ተናገረዋል።
Nov 11, 2025 474
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ስርዓቱን ከዓለም የአየር ንብረት ፣ የቴክኖሎጂ፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ለውጥ ጋር በሚጣጣም መልኩ መቃኘት እንደሚገባ ተመላከተ። ‎ ‎34ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባኤ ባለ 12 ነጥብ አቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የትምህርቱን ሥራ ከአየር ንብረት ፣ ቴክኖሎጂና ከዓለም የፖለቲካና የኢኮኖሚ ለውጥ ጋር በሚጣጣም መልኩ መቃኘትና መተግበር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
‎ይህ ጊዜ ለውጦችን በመቋቋም ወደ እድል የሚቀይሩ ፣ አገራቸውን የሚወዱና ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ዜጎችን ለማፍራት በትጋት የምንሰራበት ወቅት መሆኑንም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
በመሆኑም‎ በየደረጃው ያሉ መምምህራን በሚያስተምሩበት ትምህርት አይነት የበቁ ሆነው በመገኘት ሙያቸውን ሊያሳድጉና ሊያስከብሩ እንደሚገባ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
በተጨማሪም ‎የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተቋቋሙበት አላማ ቅድሚያ በመስጠት ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
‎የአካል ጉዳተኞችን የመማር ማስተማር ከባቢ ምቹ ለማድረግ አገሪቱ ባላት አቅም ድጋፍ እንደሚደረግም አመልክተዋል።
‎በበኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፍትሃዊና “ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም” በሚል መሪቃል የተካሄደው 34ኛው የትምህርት ጉባኤ ባለ 12 ነጥብ አቋም መግለጫ በማውጣትም ተጠናቋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የትምህርቱን ሥራ ከአየር ንብረት ፣ ቴክኖሎጂና ከዓለም የፖለቲካና የኢኮኖሚ ለውጥ ጋር በሚጣጣም መልኩ መቃኘትና መተግበር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
‎ይህ ጊዜ ለውጦችን በመቋቋም ወደ እድል የሚቀይሩ ፣ አገራቸውን የሚወዱና ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ዜጎችን ለማፍራት በትጋት የምንሰራበት ወቅት መሆኑንም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
በመሆኑም‎ በየደረጃው ያሉ መምምህራን በሚያስተምሩበት ትምህርት አይነት የበቁ ሆነው በመገኘት ሙያቸውን ሊያሳድጉና ሊያስከብሩ እንደሚገባ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
በተጨማሪም ‎የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተቋቋሙበት አላማ ቅድሚያ በመስጠት ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
‎የአካል ጉዳተኞችን የመማር ማስተማር ከባቢ ምቹ ለማድረግ አገሪቱ ባላት አቅም ድጋፍ እንደሚደረግም አመልክተዋል።
‎በበኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፍትሃዊና “ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም” በሚል መሪቃል የተካሄደው 34ኛው የትምህርት ጉባኤ ባለ 12 ነጥብ አቋም መግለጫ በማውጣትም ተጠናቋል።
Nov 11, 2025 468
የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ የልዑካን ቡድን ከፊንላንድ የትምህርትና ባህል ሚኒስቴር ጋር ተወያየ።

(ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ ልዑካን ቡድን በፊንላንድ እያደረ ካለው የልምድ ልውውጥ ጎን ለጎን ከፊንላንድ የትምህርትና ባህል ሚኒስቴር ጋር ተወያይቷል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ በመምህራን ስልጠና ፣ በአካቶና በቅድመ ልጅነት ትምህርት ዙሪያ ከፊላንድ ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በአዲስ መልክ የተደራጀው የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲን በመምህራን ስልጠና ላይ ከሚሰሩ አቻ የፊንላንድ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በማስተሳሰር በትብብር የሚሠሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ፍላጎት ያለ መሆኑን ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም በቅድመ መደበኛ ትምህርት ተሳትፎና በትምህርት ቤት ምገባ ዙሪያ ላይ የማህበረሠቡን ተሳትፎ እና ድጋፍ ለማሳደግ በተሠሩ ስራዎች የገኙ አበረታች ውጤቶችን አስመልክቶ በክቡር ሚንስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገለጻ ተደርጓል። 

የፊንላንድ ትምህርትና ባህል ሚኒስትር H.E Mr Anders E. Adlercreutz, በበኩላቸው ፊንላንድ የትምህርት ጥራት እና ፍትሃዊነት ለማረጋገጥ የሄደችበትን ርቀትና የተገኙ ስኬቶችን አስመልክቶ ለልኡካን ቡድኑ ገለጻ አድርገዋል። 

ሁለቱም ሚኒስትሮች የመምህራን አቅም ማጎልበቻ ስራዎች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የተስማሙ ሲሆን የፊንላንድ ትምህርትና ባህል ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኩል ግብዣ ቀርቦላቸዋል።

በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወትና ሌሎች የዘርፉ አመራሮችም ተገኝተዋል።

(ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ ልዑካን ቡድን በፊንላንድ እያደረ ካለው የልምድ ልውውጥ ጎን ለጎን ከፊንላንድ የትምህርትና ባህል ሚኒስቴር ጋር ተወያይቷል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስቴሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ በመምህራን ስልጠና ፣ በአካቶና በቅድመ ልጅነት ትምህርት ዙሪያ ከፊላንድ ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በአዲስ መልክ የተደራጀው የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲን በመምህራን ስልጠና ላይ ከሚሰሩ አቻ የፊንላንድ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በማስተሳሰር በትብብር የሚሠሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ፍላጎት ያለ መሆኑን ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም በቅድመ መደበኛ ትምህርት ተሳትፎና በትምህርት ቤት ምገባ ዙሪያ ላይ የማህበረሠቡን ተሳትፎ እና ድጋፍ ለማሳደግ በተሠሩ ስራዎች የገኙ አበረታች ውጤቶችን አስመልክቶ በክቡር ሚንስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገለጻ ተደርጓል። 

የፊንላንድ ትምህርትና ባህል ሚኒስትር H.E Mr Anders E. Adlercreutz, በበኩላቸው ፊንላንድ የትምህርት ጥራት እና ፍትሃዊነት ለማረጋገጥ የሄደችበትን ርቀትና የተገኙ ስኬቶችን አስመልክቶ ለልኡካን ቡድኑ ገለጻ አድርገዋል። 

ሁለቱም ሚኒስትሮች የመምህራን አቅም ማጎልበቻ ስራዎች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የተስማሙ ሲሆን የፊንላንድ ትምህርትና ባህል ሚኒስትሩ ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኩል ግብዣ ቀርቦላቸዋል።

በውይይቱ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወትና ሌሎች የዘርፉ አመራሮችም ተገኝተዋል።

Nov 07, 2025 537
የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ ልዑካን ቡድን በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተሳትፏል።

በትምህርት ሚኒስትሩ የተመራ የልዑካን ቡድን አባላት በሳማርካንድ፣ ኡዝቤኪስታን ሪፐብሊክ በተካሄደው 43ኛው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተሳትፎ አድርጓል።
በዚህ የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) 43ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት በዩኔስኮ ዘርፎች ያከናወነችውን ተግባራት አብራርተዋል።
በዚህም ከትምህርት፣ ከባሕል፣ ከአየር ንብረት ለውጥ እና ከብዝሃ-ሕይወት ዘርፍ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ እየሰራቻቸው ያሉ ሥራዎችን ለጉባኤው አስረድተዋል፡፡
አያይዘውም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የተነደፉ ስትራቴጂዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው ይህ የዩኔስኮ ጠቅላላ ጉባኤ በትምህርት፣ በሣይንስ፣ በባህል፣ ተግባቦትና መረጃ ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ፤ አባል ሀገራትን ለመደገፍ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መድረክ እንደሆነም ተጠቁሟል።
ክቡር ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር የሚያስችሉ ውይይቶችን አድርገዋል።
በትምህርት ሚኒስትሩ የተመራ የልዑካን ቡድን አባላት በሳማርካንድ፣ ኡዝቤኪስታን ሪፐብሊክ በተካሄደው 43ኛው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተሳትፎ አድርጓል።
በዚህ የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) 43ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ዓመታት በዩኔስኮ ዘርፎች ያከናወነችውን ተግባራት አብራርተዋል።
በዚህም ከትምህርት፣ ከባሕል፣ ከአየር ንብረት ለውጥ እና ከብዝሃ-ሕይወት ዘርፍ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ እየሰራቻቸው ያሉ ሥራዎችን ለጉባኤው አስረድተዋል፡፡
አያይዘውም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የ2030 ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የተነደፉ ስትራቴጂዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል።
በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው ይህ የዩኔስኮ ጠቅላላ ጉባኤ በትምህርት፣ በሣይንስ፣ በባህል፣ ተግባቦትና መረጃ ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ፤ አባል ሀገራትን ለመደገፍ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መድረክ እንደሆነም ተጠቁሟል።
ክቡር ሚኒስትሩ ከጉባኤው ጎን ለጎንም ከተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር የሚያስችሉ ውይይቶችን አድርገዋል።
Nov 07, 2025 479
የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ የልዑካን ቡድን በፊንላንድ ጥናታዊ ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።

ከፊላንድ መንግስት በተላከላቸው ግብዣ መሠረት በክቡር ሚኒስትሩ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በፊንላንድ ጥናታዊ ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።
በዚህ ጉብኝትም የትምህርት ሚኒስትሩን ጨምሮ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወትና የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ እኩኝ ኡኬሎ እየተሳተፉ ይገኛል።
የልዑካን ቡድኑ በቆይታው ከፊንላንድ የትምህርትና ባህል ሚኒስትር፣ ከፊላንድ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከብሔራዊ የትምህርት ማዕከል፣ እንዲሁም ከሂልሲንኪ ዩኒቨርሲቲና ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችን ጋር ውይይት የሚያደርጉ ይሆናል።
በዚህ ጥናታዊና የልምድ ልውውጥ ጉብኝት ወቅትም በኢትዮጵያና በፊላንድ የትምህርት ተቋማት ሊኖር ስለሚገባው ትብብር እና የፋይናንስ ድጋፍ ተጠናክሮ በሚቀጥልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከፊላንድ መንግስት በተላከላቸው ግብዣ መሠረት በክቡር ሚኒስትሩ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በፊንላንድ ጥናታዊ ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።
በዚህ ጉብኝትም የትምህርት ሚኒስትሩን ጨምሮ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወትና የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ እኩኝ ኡኬሎ እየተሳተፉ ይገኛል።
የልዑካን ቡድኑ በቆይታው ከፊንላንድ የትምህርትና ባህል ሚኒስትር፣ ከፊላንድ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከብሔራዊ የትምህርት ማዕከል፣ እንዲሁም ከሂልሲንኪ ዩኒቨርሲቲና ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችን ጋር ውይይት የሚያደርጉ ይሆናል።
በዚህ ጥናታዊና የልምድ ልውውጥ ጉብኝት ወቅትም በኢትዮጵያና በፊላንድ የትምህርት ተቋማት ሊኖር ስለሚገባው ትብብር እና የፋይናንስ ድጋፍ ተጠናክሮ በሚቀጥልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Nov 07, 2025 526
Recent News
Follow Us