ዜና

የሀገር ውስጥ ዜና

በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ቡኢ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ።

መርሃ ግብሩን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል(ዶ/ር) እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ስርዓቱ የገጠመንን የሞራል ስብራት ለማስተካከል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
እንደ ሀገር በፍጥነት ማደግ ከፈለግን በትምህርት ላይ ትኩረት አድርገን መሥራት አለብን፤ በዚህም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት በሀሉም አካባቢ ለመሥጠት በኢትዮጵያ ያሉ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
እስከዛው ድረስ ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑ የነገ ሀገር መሪዎችን ለማፍራት ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ትምህርት እያስጀመርን እንገኛለን ያሉ ሲሆን ።
ይህ ፕሮጀክት ወደፊት የሀገር መሪ የሚሆኑ ልጆችን ማፍራት አለብን በሚል የተቋቋመ በመሆኑ ይህንን ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ በቁርጠኝነት መሥራት አለበት ብለዋል።
ተማሪዎችም በአለም ተወዳድረን ከማንም ሀገር እኩል መሆናችንን ማሳየት የምንችለው በእናንተ ነው፤ ለዛም ነው ከሁሉም የሀገራችን ክፍል አወዳድረን በመቀበል ልዩ ትኩረት ሰጥተን እያስተማርናችሁ ያለው ያሉ ሲሆን ያገኛችሁት እድል ማንም ያላገኘው በመሆኑ ጠንክራችሁ ለተያዘው ራዕይ መሳካት መማር አለባችሁ ሲሉም አሳስበዋል።
አክለውም መምህራንና የትምህርት ቤቱ አስተዳደርም ከተማሪዎች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት የመማር ማስተማር ብቻ ሳይሆን ቤተሰባዊና ልጆቹ ሰው ሆነው እንዲወጡ የማድረግ ጭምር በመሆኑ ይህንን ታሪካዊ ሀገራዊ ሀላፊነት እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው በእነዚህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎችና መምህራን ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ በመሆኑ ትርጉሙን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ወደ አደጉት ሀገራት ደረጃ ለማሳደግ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባር ፣ እርስ በርስ በመረዳዳት እንዲሁም ከማንም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ጠንክረው መማር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ባሉ የሪፎርም ተግባራት ውጤት ማየት ጀምረናል ያሉ ሲሆን ለዚህ አዳሪ ትምህርት ቤት ሰኬታማነትም አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እናደርጋለን ብለዋል።
በመድረኩም ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና ልምድ በመስጠት ድጋፍ ላደረገው የሀይሌ ማናስ አካዳሚ ምሰጋና ቀርቧል።
መርሃ ግብሩን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል(ዶ/ር) እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ስርዓቱ የገጠመንን የሞራል ስብራት ለማስተካከል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
እንደ ሀገር በፍጥነት ማደግ ከፈለግን በትምህርት ላይ ትኩረት አድርገን መሥራት አለብን፤ በዚህም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት በሀሉም አካባቢ ለመሥጠት በኢትዮጵያ ያሉ ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
እስከዛው ድረስ ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑ የነገ ሀገር መሪዎችን ለማፍራት ከመላ ሀገሪቱ ተመርጠው የሚገቡባቸው ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ትምህርት እያስጀመርን እንገኛለን ያሉ ሲሆን ።
ይህ ፕሮጀክት ወደፊት የሀገር መሪ የሚሆኑ ልጆችን ማፍራት አለብን በሚል የተቋቋመ በመሆኑ ይህንን ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ በቁርጠኝነት መሥራት አለበት ብለዋል።
ተማሪዎችም በአለም ተወዳድረን ከማንም ሀገር እኩል መሆናችንን ማሳየት የምንችለው በእናንተ ነው፤ ለዛም ነው ከሁሉም የሀገራችን ክፍል አወዳድረን በመቀበል ልዩ ትኩረት ሰጥተን እያስተማርናችሁ ያለው ያሉ ሲሆን ያገኛችሁት እድል ማንም ያላገኘው በመሆኑ ጠንክራችሁ ለተያዘው ራዕይ መሳካት መማር አለባችሁ ሲሉም አሳስበዋል።
አክለውም መምህራንና የትምህርት ቤቱ አስተዳደርም ከተማሪዎች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት የመማር ማስተማር ብቻ ሳይሆን ቤተሰባዊና ልጆቹ ሰው ሆነው እንዲወጡ የማድረግ ጭምር በመሆኑ ይህንን ታሪካዊ ሀገራዊ ሀላፊነት እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው በእነዚህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎችና መምህራን ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ በመሆኑ ትርጉሙን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ወደ አደጉት ሀገራት ደረጃ ለማሳደግ በእውቀት ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባር ፣ እርስ በርስ በመረዳዳት እንዲሁም ከማንም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ጠንክረው መማር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል (ዶ/ር) በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ባሉ የሪፎርም ተግባራት ውጤት ማየት ጀምረናል ያሉ ሲሆን ለዚህ አዳሪ ትምህርት ቤት ሰኬታማነትም አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እናደርጋለን ብለዋል።
በመድረኩም ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና ልምድ በመስጠት ድጋፍ ላደረገው የሀይሌ ማናስ አካዳሚ ምሰጋና ቀርቧል።
Dec 27, 2025 126
የሀገር ውስጥ ዜና

ለፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የወደፊቱ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ሰብዕና የሚገነባባቸው ተቋማት መሆናቸው ተመላከተ፤ የቦንጋ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

በአዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ እንደገለጹት አዳሪ ትምህርት ቤቶች የነገዎቹ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ስብዕና የሚገነባባቸው ቦታዎች ናቸው።
‎ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው ትምህርት ከማቅረብ ጎን ለጎን በጥሩ ባህሪ የተገነቡ ፣ሥነምግባር የተላበሱና በሙያቸው የላቀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዜጎች የሚፈሩባቸው ማዕከላት መሆናቸውንም ክቡር አቶ ኮራ አስገንዝበዋል።
‎የትምህርት ቤቶች ትኩረት በአብዛኛው የአካዳሚክ ዕውቀትን በማስተላለፍ ላይ ያተኮረ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከንድፈ ሀሳብ እውቀት ባሻገር የተማሩትን ወደ ተግባር በመለወጥ የማህበረሰቡን ችግር መፍታት የሚችሉ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
‎በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች መማር ያለባቸው ለዕውቀት ብቻ ሳይሆን ያወቁትን ወደ ተግባር ለመቀየር፣ ለመለወጥ፣ ከሌላው ጋር አብሮ መኖር የመሳሰሉ የትምህርት ምሶሶዎችን በማሟላት ሙሉ ሰው መሆን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
‎የቦንጋ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችም በትምህርት ቤቱ በሚኖራቸው ቆይታ በመቻቻል ፣በመከባበር፣በመዋደድና አብሮ በመኖር ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ደስታ ገነሜ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ስርዓቱ ላይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት የነገ አገር ተረካቢዎችን ለማፍራት በልዩ ሁኔታ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች ፣ከተማሪዎች ከክልሉና ዞኑ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።
‎በመጨረሻም የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍሎች በመጎብኘትና አሻራቸውን በማኖር ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀዋል።
በአዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ እንደገለጹት አዳሪ ትምህርት ቤቶች የነገዎቹ አገር ተረካቢዎች ሁለንተናዊ ስብዕና የሚገነባባቸው ቦታዎች ናቸው።
‎ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ጥራት ያለው ትምህርት ከማቅረብ ጎን ለጎን በጥሩ ባህሪ የተገነቡ ፣ሥነምግባር የተላበሱና በሙያቸው የላቀ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ዜጎች የሚፈሩባቸው ማዕከላት መሆናቸውንም ክቡር አቶ ኮራ አስገንዝበዋል።
‎የትምህርት ቤቶች ትኩረት በአብዛኛው የአካዳሚክ ዕውቀትን በማስተላለፍ ላይ ያተኮረ መሆኑን የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከንድፈ ሀሳብ እውቀት ባሻገር የተማሩትን ወደ ተግባር በመለወጥ የማህበረሰቡን ችግር መፍታት የሚችሉ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
‎በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች መማር ያለባቸው ለዕውቀት ብቻ ሳይሆን ያወቁትን ወደ ተግባር ለመቀየር፣ ለመለወጥ፣ ከሌላው ጋር አብሮ መኖር የመሳሰሉ የትምህርት ምሶሶዎችን በማሟላት ሙሉ ሰው መሆን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
‎የቦንጋ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችም በትምህርት ቤቱ በሚኖራቸው ቆይታ በመቻቻል ፣በመከባበር፣በመዋደድና አብሮ በመኖር ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ደስታ ገነሜ በበኩላቸው የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ስርዓቱ ላይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት የነገ አገር ተረካቢዎችን ለማፍራት በልዩ ሁኔታ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች ፣ከተማሪዎች ከክልሉና ዞኑ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።
‎በመጨረሻም የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍሎች በመጎብኘትና አሻራቸውን በማኖር ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀዋል።
Dec 27, 2025 111
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በጂግጂጋ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላለፉ።

የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸው የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የጂግጂጋ የፌዴራል አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚንስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ለአጠቃላይ የት/ቤቱ ማህበረሰብ መርሃ ግብሩን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም መንግስት የትምህርት ጥራት፣ አግባብነትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታዋ በዚህ የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገኛችሁ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ታሪካዊ በሆነው መርሃ ግብር የመጀመሪያዎቹ ተዋንያን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
አያይዘውም ተማሪዎች ዓላማቸው ላይ ትኩረት በማድረግ በትምህርታቸው ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባርም ምሳሌ የሚሆኑ ዜጎች እንዲሆኑ፤ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እንደ ቤተሰብ ሆነው በታላቅ ሃላፊነት ተማሪዎችን በማገዝ ብቁ ዜጎችን እንዲያፈሩ አደራ ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር በማያያዝም እስካሁን በጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ትምህርት ቢሮ በኩል ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገድና ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተጀመሩ ስራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ በማስቀጠል ክፍተቶች እየተሞሉ ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሄድ እንዳለበት አሳስበዋል።
በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ መሃመድ አደን እና የጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ ፔሬዘዳንት ዶ/ር ሠይድ መሃመድ በመገኘት ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸው የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የጂግጂጋ የፌዴራል አዳሪ ትምህርት ቤት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚንስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ለተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ለአጠቃላይ የት/ቤቱ ማህበረሰብ መርሃ ግብሩን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም መንግስት የትምህርት ጥራት፣ አግባብነትና ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አንጻር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ነው ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታዋ በዚህ የፌደራል አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተገኛችሁ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ታሪካዊ በሆነው መርሃ ግብር የመጀመሪያዎቹ ተዋንያን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
አያይዘውም ተማሪዎች ዓላማቸው ላይ ትኩረት በማድረግ በትምህርታቸው ብቻ ሳይሆን በስነ-ምግባርም ምሳሌ የሚሆኑ ዜጎች እንዲሆኑ፤ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እንደ ቤተሰብ ሆነው በታላቅ ሃላፊነት ተማሪዎችን በማገዝ ብቁ ዜጎችን እንዲያፈሩ አደራ ብለዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከዚሁ ጋር በማያያዝም እስካሁን በጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ትምህርት ቢሮ በኩል ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገድና ግብዓቶችን በማሟላት ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተጀመሩ ስራዎችን በተጠናከረ ሁኔታ በማስቀጠል ክፍተቶች እየተሞሉ ለመማር ማስተማር ስራው ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሄድ እንዳለበት አሳስበዋል።
በማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ መሃመድ አደን እና የጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ ፔሬዘዳንት ዶ/ር ሠይድ መሃመድ በመገኘት ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
Dec 27, 2025 129
የሀገር ውስጥ ዜና

የዩኒቨርስቲ የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥን አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖራቸው እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፤

የጅማ ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ጌንት የ25 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎለታል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥናቸው አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖር እየተሰራ ይገኛል።
‎የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች እንደሀገር እሰከ 80 በመቶ የሚደርስ የክሊኒካል አገልግሎት ጫና እንዳለባቸው የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመፍታትም አየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ ለዩኒቨርስቲው ህክምና ማዕከል የተደረገው የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ሆስፒታሉ የተሻለ የህክምና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችለው ጠቅሰዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው የጅማ ዩኒቨርስቲን ልዩ ልዩ የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የጅማ ዩኒቨርስቲ ሆስፒታል ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ጌንት የ25 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎለታል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት የማስተማሪያ ሆስፒታሎች የሚመጥናቸው አሰራርና አደረጃጀት እንዲኖር እየተሰራ ይገኛል።
‎የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሎች እንደሀገር እሰከ 80 በመቶ የሚደርስ የክሊኒካል አገልግሎት ጫና እንዳለባቸው የጠቆሙት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመፍታትም አየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
‎የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ ለዩኒቨርስቲው ህክምና ማዕከል የተደረገው የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ሆስፒታሉ የተሻለ የህክምና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችለው ጠቅሰዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው የጅማ ዩኒቨርስቲን ልዩ ልዩ የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
Dec 27, 2025 108
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የወሊሶ ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ ተዘዋውረው ተመለከቱ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት የወሊሶ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበት ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
አመራሮቹ የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍል፣ የተማሪዎች ዶርም፣ የመመገቢያ አዳራሽ ፣ የአስተዳደር ህንፃና ሌሎች ግንባታዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በምልከታቸውም ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የተመለከቱ ሲሆን ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ተማሪዎችን ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የማዛወር ሥራ ይሰራል ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የወሊሶ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ እስኪደርስ ድረስ ተማሪዎች በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሀጫሉ ካምፓስ በመቀበል በዛሬው እለት የመማር ማስተማር ሥራ ማስጀመሩ ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት የወሊሶ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የደረሰበት ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
አመራሮቹ የትምህርት ቤቱን የመማሪያ ክፍል፣ የተማሪዎች ዶርም፣ የመመገቢያ አዳራሽ ፣ የአስተዳደር ህንፃና ሌሎች ግንባታዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በምልከታቸውም ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የተመለከቱ ሲሆን ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ተማሪዎችን ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ የማዛወር ሥራ ይሰራል ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የወሊሶ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ እስኪደርስ ድረስ ተማሪዎች በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሀጫሉ ካምፓስ በመቀበል በዛሬው እለት የመማር ማስተማር ሥራ ማስጀመሩ ይታወሳል።
Dec 26, 2025 121
የሀገር ውስጥ ዜና

በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የወሊሶ ፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመማር ማስተማር ሥራ የማስጀመር ሥነ ሥርዓት ተካሄደ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት፣ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) እና የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው አስጀምረዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህር ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ብቁ፣ ተወዳዳሪና ለወደፊት ለሀገሪቱ ጠንካራ መሪ ለማውጣት ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በማቋቋም ከመላ ሀገሪቱ ተማሪዎችን በመቀበል ዛሬ ትምህርት የማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሂደናል ብለዋል።
ትልቅ ስልጣኔ የነበራትና ትልቅ ሀገር መሆን የሚገባት ሀገር የምትበላውን የምትለምን ሀገር ሆና ወደ ኋላ ቀርታለች ያሉት ሚኒስትሩ።
ባለፉት የለውጥ አመታት በትንሹ በትልቁ ከመባላት ወጥተን እንዴት ሀገራችንን መለወጥ እንችላለን የሚለውን በማሰብ በትምህርት ሥርዓቱ ጠንካራ ተወዳዳሪና ብቃት ያላቸው ልጆችን ለማፍራት የሚያስችሉ ሥራወች እየተሰሩ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የሀገርን እድገት ማረጋገጥ የሚቻለው ጥራት ያለው ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ማድረስ ሲቻል በመሆኑ በገጠርም ሆነ በከተማ ሁሉም ዜጋ ጥሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም በዚህ ትምህርት ቤት የመማር እድል ያገኛችሁ ተማሪዎች በትምህርትና በእውቀት ብቻ ሳይሆን ሥነ ምግባር የተላበሳችሁ፣ ከስንፍና የተላቀቃችሁ፣ ሌላውን በመርዳት ሰው እንድትሆኑ እንፈልጋለንም ብለዋል።
ተማሪዎች ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ልጆች መሆን አለባችሁ ያሉት ሚኒስትሩ እናንተ ከመላው ኢትዮጵያ የመጣችሁ በመሆናችሁ እርስ በርስ መከባበር አንዱ የአንዱን ባህል ማክበርና መረዳዳት ይጠበቅባችኋል በማለት እንደ ሀገር አስበው በጋራ ጠንክረው መማር እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ይህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ከሌሎቹ ለየት የሚያደርገው ከአንድ አካባቢ ሳይሆን ከመላው ኢትዮጵያ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች ተመርጠው የሚማሩበት መሆኑ ነው ብለዋል።
በመሆኑም ተማሪዎች ነገ ይችን ሀገር ለመረከብ ጠንክረው መማር እንዳለባቸውና መምህራንም የነገ ሀገር ተረካቢ ተማሪዎችን የማብቃት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ደግሞ ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ የመጀመሪያዎቹን የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ዛሬ የማስጀመሪያ ፕሮግራም በመካሄዱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው ሰው ለማድረግ ከመምህራን ጋር በመሆን የተሰጣቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት፣ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) እና የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው አስጀምረዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህር ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ብቁ፣ ተወዳዳሪና ለወደፊት ለሀገሪቱ ጠንካራ መሪ ለማውጣት ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በማቋቋም ከመላ ሀገሪቱ ተማሪዎችን በመቀበል ዛሬ ትምህርት የማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሂደናል ብለዋል።
ትልቅ ስልጣኔ የነበራትና ትልቅ ሀገር መሆን የሚገባት ሀገር የምትበላውን የምትለምን ሀገር ሆና ወደ ኋላ ቀርታለች ያሉት ሚኒስትሩ።
ባለፉት የለውጥ አመታት በትንሹ በትልቁ ከመባላት ወጥተን እንዴት ሀገራችንን መለወጥ እንችላለን የሚለውን በማሰብ በትምህርት ሥርዓቱ ጠንካራ ተወዳዳሪና ብቃት ያላቸው ልጆችን ለማፍራት የሚያስችሉ ሥራወች እየተሰሩ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
የሀገርን እድገት ማረጋገጥ የሚቻለው ጥራት ያለው ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ማድረስ ሲቻል በመሆኑ በገጠርም ሆነ በከተማ ሁሉም ዜጋ ጥሩ የትምህርት ዕድል እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም በዚህ ትምህርት ቤት የመማር እድል ያገኛችሁ ተማሪዎች በትምህርትና በእውቀት ብቻ ሳይሆን ሥነ ምግባር የተላበሳችሁ፣ ከስንፍና የተላቀቃችሁ፣ ሌላውን በመርዳት ሰው እንድትሆኑ እንፈልጋለንም ብለዋል።
ተማሪዎች ልዩ ተሰጥኦ ያላችሁ ልጆች መሆን አለባችሁ ያሉት ሚኒስትሩ እናንተ ከመላው ኢትዮጵያ የመጣችሁ በመሆናችሁ እርስ በርስ መከባበር አንዱ የአንዱን ባህል ማክበርና መረዳዳት ይጠበቅባችኋል በማለት እንደ ሀገር አስበው በጋራ ጠንክረው መማር እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው ይህ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ከሌሎቹ ለየት የሚያደርገው ከአንድ አካባቢ ሳይሆን ከመላው ኢትዮጵያ ብቃት ያላቸው ተማሪዎች ተመርጠው የሚማሩበት መሆኑ ነው ብለዋል።
በመሆኑም ተማሪዎች ነገ ይችን ሀገር ለመረከብ ጠንክረው መማር እንዳለባቸውና መምህራንም የነገ ሀገር ተረካቢ ተማሪዎችን የማብቃት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ደግሞ ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ የመጀመሪያዎቹን የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ዛሬ የማስጀመሪያ ፕሮግራም በመካሄዱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው ሰው ለማድረግ ከመምህራን ጋር በመሆን የተሰጣቸውን ኃላፊነት እንደሚወጡ ቃል ገብተዋል።
Dec 26, 2025 94
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አደረጉ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ ህይወት ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት ዓመታት የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋፋት ቢሰራም ከትምህርት ጥራት አንፃር የትምህርት ሥርዓቱ ችግር ውስጥ ገብቶ ቆይቷል ብለዋል።
በተጨማሪም ትምህርትና ፖለቲካ በመደበላለቃቸው የትምህርት ተቋማት የፖለቲካ ፍላጎት ማስጠበቂያ ተደርገው መቆየታቸውንም ሌላው ችግር መሆኑን አንስተዋል።
አሁን አለም እየሄደች ባለችበት መንገድ ተቋቁመን አብረን ለመቀጠልና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት በዚህ መንገድ መቀጠል ስለማይቻል ችግሩን ለመፍታት በትምህርት ዘርፉ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው እየተተገበሩ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይ ዩኒቨርሲቲዎች እውነትና እውቀት የሚፈልቅባቸው በነፃነት ውይይት የሚደረግባቸው ዩኒቨርሳል ተቋማት መሆናቸውን ያነሱ ሲሆን፤
ዩኒቨርሲቲዎች ኢትዮጵያ ባላት ፀጋዎች ዙሪያ ትርጉም ያላቸው ፈጠራ እና ጥናትና ምርምር የሚደረግባቸው ተቋማት ሊሆኑ እንደሚገባ ጠቅሰው ተቋማቱም ለስራዎቻቸው የሚበረታቱበት ሥርዓት መፍጠር ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን የዩኒቨርሲቲ አመራር ምደባም ከመንደር ወጥቶ በውድድር እንዲሆን እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው እየተተገበሩ ሲሆን ዘላቂነታቸውን ለማረጋገጥ አብዛኞቹን ወደ ፖሊሲና ውጤታማነት እየተቀየሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ከተመሠረተ ጀምሮ በርካታ ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን የተናሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባይሳ ለታ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ውጤታማ እንዲሆን የበለጠ ለጥራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ ህይወት ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት ዓመታት የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋፋት ቢሰራም ከትምህርት ጥራት አንፃር የትምህርት ሥርዓቱ ችግር ውስጥ ገብቶ ቆይቷል ብለዋል።
በተጨማሪም ትምህርትና ፖለቲካ በመደበላለቃቸው የትምህርት ተቋማት የፖለቲካ ፍላጎት ማስጠበቂያ ተደርገው መቆየታቸውንም ሌላው ችግር መሆኑን አንስተዋል።
አሁን አለም እየሄደች ባለችበት መንገድ ተቋቁመን አብረን ለመቀጠልና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት በዚህ መንገድ መቀጠል ስለማይቻል ችግሩን ለመፍታት በትምህርት ዘርፉ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው እየተተገበሩ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይ ዩኒቨርሲቲዎች እውነትና እውቀት የሚፈልቅባቸው በነፃነት ውይይት የሚደረግባቸው ዩኒቨርሳል ተቋማት መሆናቸውን ያነሱ ሲሆን፤
ዩኒቨርሲቲዎች ኢትዮጵያ ባላት ፀጋዎች ዙሪያ ትርጉም ያላቸው ፈጠራ እና ጥናትና ምርምር የሚደረግባቸው ተቋማት ሊሆኑ እንደሚገባ ጠቅሰው ተቋማቱም ለስራዎቻቸው የሚበረታቱበት ሥርዓት መፍጠር ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን የዩኒቨርሲቲ አመራር ምደባም ከመንደር ወጥቶ በውድድር እንዲሆን እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው እየተተገበሩ ሲሆን ዘላቂነታቸውን ለማረጋገጥ አብዛኞቹን ወደ ፖሊሲና ውጤታማነት እየተቀየሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ከተመሠረተ ጀምሮ በርካታ ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን የተናሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባይሳ ለታ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ውጤታማ እንዲሆን የበለጠ ለጥራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
Dec 26, 2025 118
የሀገር ውስጥ ዜና

ሥራ ፈጣሪነትንና ፈጠራን በማስተማርና በማበረታታት ምሩቃንን ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት ማሸጋገር እንደሚገባቸው ተመላከተ

ትምህርት ሚኒስቴር ከኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች የተማሪዎችን ሀሳብና ፈጠራ በመደገፍ ምሩቃን ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
‎ዩኒቨርስቲዎች በአብዛኛው በማስተማር ስራ ላይ እንደሚያተኩሩ ያነሱት ሚኒስትር ዳኤታው ነገር ግን የሥራ ፈጠራ ሀሳቦችን ማመንጨትና ወደ ተግባር በመቀየር የማህበረሰቡን ህይወት መለወጥና ኢኮኖሚውን ማሳደግ እንደሚ ጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
‎ይህ ከኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር የተደረገው የመግባቢያ ስምምነትም የተማሪዎችና የመምህራን የፈጠራ ሀሳቦችን በመደገፍ ክፍተቶች ለመሙላትና የንግድ ፈጠራ ስራዎችን ለማበረታታት እንደሚያስችል ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።
‎የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሐሰን ሁሴን (ዶ/ር) ስምምነቱ የፈጠራና ኢኖቬሽን ስራዎችን በማበረታታት ችግሮችን ወደ እድል ለመቀየር እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የመግባቢያ ስምምነቱ ትምህርት ሚኒስቴር የቢዝነስ ቴክኖሎጂ ፣ ኢኖቬሽንና ኢንኩቤሽን ማዕከላት በማቋቋም እያከናወነ የሚገኘውን የሪፎርም ሥራ እንደሚያጠናክረውም የተገለጸ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሥራ ፈጠራ ክህሎትን በማስተማርና የፈጠራ ሀሳቦች እንዲጎለብቱ በትኩረት መሥራት ይጠበቅባቸዋልም ተብሏል።
‎የስምምነት ሰነዱ የትምህርት ሚኒስቴርና የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በተገኙበት ተፈርሟል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች የተማሪዎችን ሀሳብና ፈጠራ በመደገፍ ምሩቃን ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
‎ዩኒቨርስቲዎች በአብዛኛው በማስተማር ስራ ላይ እንደሚያተኩሩ ያነሱት ሚኒስትር ዳኤታው ነገር ግን የሥራ ፈጠራ ሀሳቦችን ማመንጨትና ወደ ተግባር በመቀየር የማህበረሰቡን ህይወት መለወጥና ኢኮኖሚውን ማሳደግ እንደሚ ጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።
‎ይህ ከኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር የተደረገው የመግባቢያ ስምምነትም የተማሪዎችና የመምህራን የፈጠራ ሀሳቦችን በመደገፍ ክፍተቶች ለመሙላትና የንግድ ፈጠራ ስራዎችን ለማበረታታት እንደሚያስችል ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።
‎የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሐሰን ሁሴን (ዶ/ር) ስምምነቱ የፈጠራና ኢኖቬሽን ስራዎችን በማበረታታት ችግሮችን ወደ እድል ለመቀየር እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የመግባቢያ ስምምነቱ ትምህርት ሚኒስቴር የቢዝነስ ቴክኖሎጂ ፣ ኢኖቬሽንና ኢንኩቤሽን ማዕከላት በማቋቋም እያከናወነ የሚገኘውን የሪፎርም ሥራ እንደሚያጠናክረውም የተገለጸ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሥራ ፈጠራ ክህሎትን በማስተማርና የፈጠራ ሀሳቦች እንዲጎለብቱ በትኩረት መሥራት ይጠበቅባቸዋልም ተብሏል።
‎የስምምነት ሰነዱ የትምህርት ሚኒስቴርና የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በተገኙበት ተፈርሟል።
Dec 25, 2025 136
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ አዲስ ከተመደቡት የጣሊያን አምባሳደር ጋር ተወያዩ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ አዲስ የተመደቡትን የጣሊያን አምባሳደር H.E. Sem Fabrizi በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ እና ጣሊያን ለረጅም ጊዜ የቆየ ትብብር ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ይህ ግንኙነታቸው የበለጠ እየዳበረ መምጣቱን ተናግረዋል።
በትምህርት ዘርፉ ኢትዮጵያ እየተገበረቻቸው ያሉ ዋና ዋና የሪፎርም ተግባራትን ለአምባሳደሩ ያብራሩት ክቡር ሚኒስትሩ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል የትምህርት ሥርዓት ለመዘርጋት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑም ገልጸውላቸዋል።
በኢትዮጵያ አዲሱ የጣሊያን አምባሳደር H.E. Sem Fabrizi በበኩላቸው ጣሊያን በትምህርት ዘርፉ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ስትሰራ መቆየቷን ጠቅሰው ይህንን ትብብር በማሻሻል ወደ ላቀ ደርጃ ማድረስ እንደሚፈልጉ ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
በተለይም በአጠቃላይ ትምህርት፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በኢትዮጵያና በጣሊያን ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የሚረግ ግንኙነትና በነጻ የትምህርት እድል ዙሪያ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳላቸው አምባሳደሩ ተናግረዋል።
በዚህም መሠረት በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተማሪዎችና የመምህራን ልውውጥ እና የጋራ የምርምር ስራዎች ለመስራት ፣ የጋራ ዲግሪዎች የሚሰጡበት የትምህርት መርሃግብር ላይ ለመስማማት እና እንደ ኢራስመስ ፕላስ እና ሆራይዘን አውሮፓ ባሉ ዋና ዋና የጋራ ባለብዙ ወገን ፕሮግራሞች ውስጥ ትብብር ለማድረግ ተስማምተዋል።
በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ በጣሊያን የትምህርት ሚኒስቴርና የብቃት ሚኒስቴር 'አንድ ላይ የማደግ ፕሮጀክት ውስጥ በሁለቱ ሀገራት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና የትምህርት ተቋማት መካከል ትብብርና ልውውጥን ለማበረታታት በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ እንዲዘጋጅ ከመግባባት ደርሰዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ አዲስ የተመደቡትን የጣሊያን አምባሳደር H.E. Sem Fabrizi በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ እና ጣሊያን ለረጅም ጊዜ የቆየ ትብብር ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ይህ ግንኙነታቸው የበለጠ እየዳበረ መምጣቱን ተናግረዋል።
በትምህርት ዘርፉ ኢትዮጵያ እየተገበረቻቸው ያሉ ዋና ዋና የሪፎርም ተግባራትን ለአምባሳደሩ ያብራሩት ክቡር ሚኒስትሩ ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል የትምህርት ሥርዓት ለመዘርጋት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑም ገልጸውላቸዋል።
በኢትዮጵያ አዲሱ የጣሊያን አምባሳደር H.E. Sem Fabrizi በበኩላቸው ጣሊያን በትምህርት ዘርፉ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ስትሰራ መቆየቷን ጠቅሰው ይህንን ትብብር በማሻሻል ወደ ላቀ ደርጃ ማድረስ እንደሚፈልጉ ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
በተለይም በአጠቃላይ ትምህርት፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በኢትዮጵያና በጣሊያን ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የሚረግ ግንኙነትና በነጻ የትምህርት እድል ዙሪያ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳላቸው አምባሳደሩ ተናግረዋል።
በዚህም መሠረት በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተማሪዎችና የመምህራን ልውውጥ እና የጋራ የምርምር ስራዎች ለመስራት ፣ የጋራ ዲግሪዎች የሚሰጡበት የትምህርት መርሃግብር ላይ ለመስማማት እና እንደ ኢራስመስ ፕላስ እና ሆራይዘን አውሮፓ ባሉ ዋና ዋና የጋራ ባለብዙ ወገን ፕሮግራሞች ውስጥ ትብብር ለማድረግ ተስማምተዋል።
በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ በጣሊያን የትምህርት ሚኒስቴርና የብቃት ሚኒስቴር 'አንድ ላይ የማደግ ፕሮጀክት ውስጥ በሁለቱ ሀገራት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና የትምህርት ተቋማት መካከል ትብብርና ልውውጥን ለማበረታታት በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ እንዲዘጋጅ ከመግባባት ደርሰዋል።
Dec 25, 2025 141
የሀገር ውስጥ ዜና

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመረጃ አያያዛቸውንና አስተዳደራቸውን በማሻሻል ትክክለኛ መረጃ የመስጠት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት መረጃ አያያዝና አስተዳደር ሥርዓት ለማሻሻል በትምህርት ዘርፉ እየተከናወኑ ባሉ የሪፎርም ሥራዎች ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ መደረክ አካሂዷል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት የመንግስትም ይሁን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መረጃ አያያዛቸውንና አስተዳደራቸውን በማሻሻል ትክክለኛ፣ ወቅታዊና ተዓማኒነት ያለው መረጃ ለሚመለከታቸው አካላት የመስጠት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አያይዘውም ይህ መድረክ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትምህርት ዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን እንዲያውቁ በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመረጃ አያያዝ፣ አስተዳደደርና ግልጽነት ላይ ተመጣጣኝ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የትምህርት መረጃ አመራርና አይሲቲ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰብስብ ለማ በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚፈለጉ መረጃዎችን ትምህርት ሚኒስቴር ወደ አበለጸገው የከፍተኛ ትምህርት መረጃ አስተዳደር ሥርዓት (HEMIS) በወቅቱ ካላስገቡ የተተነተነ ሀገራዊ መረጃ ለሀገራዊ ተልዕኮም ሆነ ለባለድርሻ አካላት ማቅረብ የማይቻል መሆኑ ጠቅሰዋል። አቶ ሰብስብ አያይዘውም መረጃን በወቅቱ ካለማስገባት ጋር ተያይዞ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዘንድ ሰፊ ክፍተት መኖሩን ጠቁመዋል፡፡
በመሆኑም በመረጃ ምዝገባ፣አያያዝና አላላክ ሂደት የተፈጠሩ ችግሮችን መፍታት እና ወደ በለጸገው የከፍተኛ ትምህርት መረጃ አስተዳደር ሥርዓት (HEMIS) ያልገቡ ተቋማትን ወደ ሥርዓቱ ማስገባት ከግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ የሚጠበቅ ሌላው ውጤት መሆኑንም በማንሳት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዚህ ረገድ የሚታየውን ክፍተት በማረም ትክክለኛ፣ ወቅታዊና ተዓማኒነት ያለው መረጃ በመስጠት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት መረጃ አያያዝና አስተዳደር ሥርዓት ለማሻሻል በትምህርት ዘርፉ እየተከናወኑ ባሉ የሪፎርም ሥራዎች ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ መደረክ አካሂዷል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት የመንግስትም ይሁን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መረጃ አያያዛቸውንና አስተዳደራቸውን በማሻሻል ትክክለኛ፣ ወቅታዊና ተዓማኒነት ያለው መረጃ ለሚመለከታቸው አካላት የመስጠት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አያይዘውም ይህ መድረክ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትምህርት ዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን እንዲያውቁ በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመረጃ አያያዝ፣ አስተዳደደርና ግልጽነት ላይ ተመጣጣኝ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የትምህርት መረጃ አመራርና አይሲቲ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰብስብ ለማ በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚፈለጉ መረጃዎችን ትምህርት ሚኒስቴር ወደ አበለጸገው የከፍተኛ ትምህርት መረጃ አስተዳደር ሥርዓት (HEMIS) በወቅቱ ካላስገቡ የተተነተነ ሀገራዊ መረጃ ለሀገራዊ ተልዕኮም ሆነ ለባለድርሻ አካላት ማቅረብ የማይቻል መሆኑ ጠቅሰዋል። አቶ ሰብስብ አያይዘውም መረጃን በወቅቱ ካለማስገባት ጋር ተያይዞ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዘንድ ሰፊ ክፍተት መኖሩን ጠቁመዋል፡፡
በመሆኑም በመረጃ ምዝገባ፣አያያዝና አላላክ ሂደት የተፈጠሩ ችግሮችን መፍታት እና ወደ በለጸገው የከፍተኛ ትምህርት መረጃ አስተዳደር ሥርዓት (HEMIS) ያልገቡ ተቋማትን ወደ ሥርዓቱ ማስገባት ከግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ የሚጠበቅ ሌላው ውጤት መሆኑንም በማንሳት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዚህ ረገድ የሚታየውን ክፍተት በማረም ትክክለኛ፣ ወቅታዊና ተዓማኒነት ያለው መረጃ በመስጠት ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል።
Dec 25, 2025 149
የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያና ህንድ መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ አስታወቁ። ‎የሦስተኛ ዲግሪ ነጻ የትምህርት እድል ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።

የከፍተኛ የትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ወዳጅነትና ትብብር እየተጠናከረ በመሄድ ላይ ነው።
‎ይፋ የሆነው የድህረ ምረቃ ትምህርትና ምርምር መርሃ ግብርም የድህረ ምረቃ ትምህርት አቅም በመገንባት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትልቅ ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ከህንድ የቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጠው የትምህርት እድል፣ የምርምር፣ ቴክኖሎጅና ፈጠራን በማሳደግ ብቁ የሰው ሀይል በጥራት ማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
‎የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው የመርሃ ግብሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን የሦስተኛ ዲግሪ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።
‎በህንድ ካሉ 8 የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በየዓመት 250 በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ 1,250 ተማሪዎች ነጻ የዶክተሬት ትምህርት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ኤባ ጠቅሰዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው የፕሮግራም አስተዳደርና አፈጻጸምን በተመለከተ በቀጣይ ከሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ጋር ምክክርና የመረጃ ልውውጥ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ በበይነ መረብ የተሳተፉት ስምንት (😎 የህንድ ቴክኖሎጂ ተቋማት ስለተቋሞቻቸውና በሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ስልጠና ስለ የሚሰጡባቸው ፕሮግራሞች አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።
የከፍተኛ የትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ወዳጅነትና ትብብር እየተጠናከረ በመሄድ ላይ ነው።
‎ይፋ የሆነው የድህረ ምረቃ ትምህርትና ምርምር መርሃ ግብርም የድህረ ምረቃ ትምህርት አቅም በመገንባት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትልቅ ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ከህንድ የቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጠው የትምህርት እድል፣ የምርምር፣ ቴክኖሎጅና ፈጠራን በማሳደግ ብቁ የሰው ሀይል በጥራት ማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
‎የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው የመርሃ ግብሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን የሦስተኛ ዲግሪ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።
‎በህንድ ካሉ 8 የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በየዓመት 250 በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ 1,250 ተማሪዎች ነጻ የዶክተሬት ትምህርት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ኤባ ጠቅሰዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው የፕሮግራም አስተዳደርና አፈጻጸምን በተመለከተ በቀጣይ ከሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ጋር ምክክርና የመረጃ ልውውጥ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ በበይነ መረብ የተሳተፉት ስምንት (😎 የህንድ ቴክኖሎጂ ተቋማት ስለተቋሞቻቸውና በሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ስልጠና ስለ የሚሰጡባቸው ፕሮግራሞች አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።
Dec 20, 2025 130
የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያና ህንድ መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ትብብር እየተጠናከረ መምጣቱን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ አስታወቁ። ‎የሦስተኛ ዲግሪ ነጻ የትምህርት እድል ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።

የከፍተኛ የትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ወዳጅነትና ትብብር እየተጠናከረ በመሄድ ላይ ነው።
‎ይፋ የሆነው የድህረ ምረቃ ትምህርትና ምርምር መርሃ ግብርም የድህረ ምረቃ ትምህርት አቅም በመገንባት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትልቅ ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ከህንድ የቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጠው የትምህርት እድል፣ የምርምር፣ ቴክኖሎጅና ፈጠራን በማሳደግ ብቁ የሰው ሀይል በጥራት ማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
‎የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው የመርሃ ግብሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን የሦስተኛ ዲግሪ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።
‎በህንድ ካሉ 8 የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በየዓመት 250 በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ 1,250 ተማሪዎች ነጻ የዶክተሬት ትምህርት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ኤባ ጠቅሰዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው የፕሮግራም አስተዳደርና አፈጻጸምን በተመለከተ በቀጣይ ከሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ጋር ምክክርና የመረጃ ልውውጥ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ በበይነ መረብ የተሳተፉት ስምንት (😎 የህንድ ቴክኖሎጂ ተቋማት ስለተቋሞቻቸውና በሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ስልጠና ስለ የሚሰጡባቸው ፕሮግራሞች አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።
የከፍተኛ የትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ ግብሩን ሲከፍቱ እንደገለጹት በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርት ዘርፍ ያለው ወዳጅነትና ትብብር እየተጠናከረ በመሄድ ላይ ነው።
‎ይፋ የሆነው የድህረ ምረቃ ትምህርትና ምርምር መርሃ ግብርም የድህረ ምረቃ ትምህርት አቅም በመገንባት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትልቅ ሽግግር ለማድረግ እንደሚያግዝ ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
ከህንድ የቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በትብብር የሚሰጠው የትምህርት እድል፣ የምርምር፣ ቴክኖሎጅና ፈጠራን በማሳደግ ብቁ የሰው ሀይል በጥራት ማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።
‎የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው የመርሃ ግብሩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢንጂነሪንግና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለውን የሦስተኛ ዲግሪ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።
‎በህንድ ካሉ 8 የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ጋር በተደረሰው ስምምነት መሠረት በየዓመት 250 በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ 1,250 ተማሪዎች ነጻ የዶክተሬት ትምህርት እድል እንደሚያገኙ ዶክተር ኤባ ጠቅሰዋል።
‎የመምህራንና የተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ በበኩላቸው የፕሮግራም አስተዳደርና አፈጻጸምን በተመለከተ በቀጣይ ከሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ጋር ምክክርና የመረጃ ልውውጥ እንደሚደረግ ተናግረዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ በበይነ መረብ የተሳተፉት ስምንት (😎 የህንድ ቴክኖሎጂ ተቋማት ስለተቋሞቻቸውና በሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ስልጠና ስለ የሚሰጡባቸው ፕሮግራሞች አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
‎በፕሮግራሙ ላይ ከሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ ፕሬዚዳንቶችና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ተገኝተዋል።
Dec 20, 2025 143
የሀገር ውስጥ ዜና

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተደረገላቸው አቀባበል

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተደረገላቸው አቀባበል

የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተደረገላቸው አቀባበል

Dec 20, 2025 159
የሀገር ውስጥ ዜና

የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ-ገዝ አድርጎ መልሶ በማቋቋም ሂደት ውስጥ ያሉ መልካም አጋጣሚዎችና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሄደ።

ምክክሩ በቀጣይ ራስ ገዝ ሆነው የሚቋቋሙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለሚያደርጉት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ግብዓት የሚሆኑ የሽግግር ረቂቅ መመሪያ ላይ ያተኮረ እንደሆነም ተመላክቷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መርሃ ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት በትምህርት ዘርፉ በመከናወን ላይ ያሉ የሪፎርም ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው አብራርተዋል።
የተቋማት ስኬትም ይሁን ውድቀት በዩኒቨርሲቲው አመራርና ማህበረሰብ ላይ የሚወድቅ መሆኑን በመገንዘብ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በቁርጠኝነት በማስፈጸም ዩኒቨርሲቲዎች ብቃት ያለው ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት የሚያስችሉ ተቋማት እንዲሆኑ ማድረግ እንደሚገባም አክለው ገልጸዋል።
በዚህም ረገድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረውን የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የማድረግ ሂደት የተገኙ ተሞክሮዎችና ተግዳሮቶችን በሚገባ በመለየት በመጪው አመት ራስ ገዝ ሆነው የሚቋቋሙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገጥማቸውን ጫና በመቋቋም ለእውነትና እውቀት የቆሙና የማይገፋ ጠንካራ ተቋም ሆነው ለመውጣት አስፈላጊውን ጥረት ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሀሳብ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ አድርጎ መልሶ የማቋቋም ሂደቶችና በራስ ገዝነት የሚገኙ ቱሩፋቶችን አንስተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባደረጉት ገለጻ ተቋማት ራስ ገዝ ሆነው ሲቋቋሙ የሀገርና የማህበረሰብ እምነትና አደራ ተጥሎባቸው መሆኑን በመረዳት የተቀመጡ ግቦችን ከስኬት ለማድረስ በጋራ መስራት እንደሚገባ አብራርተዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ ገዝነት ሽግግር የተዘጋጀውን ረቂቅ መመሪያ ለውይይት መነሻ አቅርበዋል።
ረቂቅ ሰነዱ ለራስ ገዝነት ሽግግር የሚያበቁ መስፈርቶችና ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችን የተካተተበት ሲሆን ዩኒቨርሲቲዎች በዚህ ረቂቅ መመሪያ እየተመዘኑ ሽግግር የሚያደርጉ በመሆኑ በተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው ማብራሪያና ምላሽ ተሠጥቶባቸዋል።
በቀጣይ ራስ ገዝ በመሆን ለሚቋቋሙ ዩኒቨርሲቲዎች ተሞክሮ እንዲሆን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግርን የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ወይይት ተደርጎበታል።
ምክክሩ በቀጣይ ራስ ገዝ ሆነው የሚቋቋሙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ለሚያደርጉት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ግብዓት የሚሆኑ የሽግግር ረቂቅ መመሪያ ላይ ያተኮረ እንደሆነም ተመላክቷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መርሃ ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት በትምህርት ዘርፉ በመከናወን ላይ ያሉ የሪፎርም ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው አብራርተዋል።
የተቋማት ስኬትም ይሁን ውድቀት በዩኒቨርሲቲው አመራርና ማህበረሰብ ላይ የሚወድቅ መሆኑን በመገንዘብ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በቁርጠኝነት በማስፈጸም ዩኒቨርሲቲዎች ብቃት ያለው ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት የሚያስችሉ ተቋማት እንዲሆኑ ማድረግ እንደሚገባም አክለው ገልጸዋል።
በዚህም ረገድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረውን የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የማድረግ ሂደት የተገኙ ተሞክሮዎችና ተግዳሮቶችን በሚገባ በመለየት በመጪው አመት ራስ ገዝ ሆነው የሚቋቋሙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገጥማቸውን ጫና በመቋቋም ለእውነትና እውቀት የቆሙና የማይገፋ ጠንካራ ተቋም ሆነው ለመውጣት አስፈላጊውን ጥረት ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሀሳብ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ አድርጎ መልሶ የማቋቋም ሂደቶችና በራስ ገዝነት የሚገኙ ቱሩፋቶችን አንስተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባደረጉት ገለጻ ተቋማት ራስ ገዝ ሆነው ሲቋቋሙ የሀገርና የማህበረሰብ እምነትና አደራ ተጥሎባቸው መሆኑን በመረዳት የተቀመጡ ግቦችን ከስኬት ለማድረስ በጋራ መስራት እንደሚገባ አብራርተዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ ገዝነት ሽግግር የተዘጋጀውን ረቂቅ መመሪያ ለውይይት መነሻ አቅርበዋል።
ረቂቅ ሰነዱ ለራስ ገዝነት ሽግግር የሚያበቁ መስፈርቶችና ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችን የተካተተበት ሲሆን ዩኒቨርሲቲዎች በዚህ ረቂቅ መመሪያ እየተመዘኑ ሽግግር የሚያደርጉ በመሆኑ በተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው ማብራሪያና ምላሽ ተሠጥቶባቸዋል።
በቀጣይ ራስ ገዝ በመሆን ለሚቋቋሙ ዩኒቨርሲቲዎች ተሞክሮ እንዲሆን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግርን የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ወይይት ተደርጎበታል።
Dec 20, 2025 176
Recent News
Follow Us