የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተጀመሩ ሁሉ አቀፍ የሪፎርም ስራዎች በተቀናጀ የህዝብ ግንኙነት ስራ ሊደገፉ እንደሚገባ ተገለጸ፤ የዩኒቨርስቲ የህዝብ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚዎች ፎረም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ ይገኛል።

በትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች የሪፎሮም ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ በማጀብ ለማህበረሰቡ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ማድረስ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ እውቀት የሚገበይባቸውና ሀሳብ በነጻነት የሚራመድባቸው ተቋማት መሆናቸውንም ገልጸዋል።
አክለውም በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራት ተደራሽነት፣ተገቢነት እና ፍትሃዊነት የማረጋገጥ ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ ማጀብ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ቦጋለ ከዚሁ ጋር አያይዘው እንደገለጹት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሃላፊዎች ሙያቸውን በሚገባ አውቀው የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ አበርክቶ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸው የትምህርት ሚኒስቴርም በማንኛውም ጊዜ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ኢንጅነር ቦጋለ ገ/ማርያም በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ፎረም መረጃዎችን ለመለዋወጥ፣ ግንኙነትን ለማጠናከርና ተሞክሮዎችን ለመቀመር እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የፎረሙ ተሳታፊዎች በዩኒቨርስቲው በሚኖራቸው ቆይታ መልካም ተሞክሮዎቹን እንደሚያጋሩና ከሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም ጠንካራ ልምዶችን እንዲቀስሙ እድል እንደሚፈጥርላቸው ጠቅሰዋል፤
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን(ዶ/ር) በበኩላቸው የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ከጊዜ ወደ ጊዜ በቴክኖሎጂ እየተራቀቀ በመምጣቱ ይህን የተረዳና ከጊዜው ጋር የሚራመድ ኮሙኒኬሽን መተግበር እንደሚገባ ገልጸዋል።
በፎረሙ ላይ ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ እንደገለጹት ዩኒቨርስቲዎች የሪፎሮም ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ በማጀብ ለማህበረሰቡ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ማድረስ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ እውቀት የሚገበይባቸውና ሀሳብ በነጻነት የሚራመድባቸው ተቋማት መሆናቸውንም ገልጸዋል።
አክለውም በትምህርት ዘርፉ የትምህርት ጥራት ተደራሽነት፣ተገቢነት እና ፍትሃዊነት የማረጋገጥ ስራዎችን በህዝብ ግንኙነት ስራ ማጀብ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ቦጋለ ከዚሁ ጋር አያይዘው እንደገለጹት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሃላፊዎች ሙያቸውን በሚገባ አውቀው የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ አበርክቶ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸው የትምህርት ሚኒስቴርም በማንኛውም ጊዜ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ኢንጅነር ቦጋለ ገ/ማርያም በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ፎረም መረጃዎችን ለመለዋወጥ፣ ግንኙነትን ለማጠናከርና ተሞክሮዎችን ለመቀመር እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የፎረሙ ተሳታፊዎች በዩኒቨርስቲው በሚኖራቸው ቆይታ መልካም ተሞክሮዎቹን እንደሚያጋሩና ከሌሎች ዩኒቨርስቲዎችም ጠንካራ ልምዶችን እንዲቀስሙ እድል እንደሚፈጥርላቸው ጠቅሰዋል፤
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን(ዶ/ር) በበኩላቸው የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ከጊዜ ወደ ጊዜ በቴክኖሎጂ እየተራቀቀ በመምጣቱ ይህን የተረዳና ከጊዜው ጋር የሚራመድ ኮሙኒኬሽን መተግበር እንደሚገባ ገልጸዋል።
በፎረሙ ላይ ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
Apr 05, 2025 116
የሀገር ውስጥ ዜና

የአገሪቱ ሁለንተናዊ እድገት መሰረትና ደጋፊ ለሆነው የትምህርት ዘርፍ ውጤታማነት በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ፤

“ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል ርዕስ ባለፉት ሰባት ዓመታት የለውጥ ስኬቶች ዙሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች ውይይት አካሂደዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ውይይቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ዘርፉ የአገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እድገት መሰረት በመሆኑ በቁጭትና በእልህ በመስራት የሚፈለገው ለውጥ እንዲመጣ መረባረብ ይገባል፡፡
በአገሪቱ ባለፉት ሰባት አመታት በለውጥ ጊዜ የሚጠበቁ በርካታ ተግዳሮቶች የገጠሙና አሁንም ያለተሻገርናቸው ፈተናዎች ቢኖሩም የትምህርት ዘርፉን ጨምሮ በየዘርፉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን አስረድተዋል፡፡
የለውጡ ጊዜ ማህበራዊ ሚዲያ ቀውስ የነገሰበት ፣ በዓለማችን አዲስ ስርዓት እተወለደ ያለበትና ልዩ ልዩ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች የተዛቡበት እና አስቸጋሪ ወቅት መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
በመሆኑም ችግሮችና ፈተናዎችን በጽናት በመቋቋም በቁጭት መስራትና አገሪቱንም ከእርዳታ ጠባቂነትና ከኋላ ቀርነት ማላቀቅና የህዝቦቿን ክብርና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲን ለማስፈን እና ከአድልዎ የጸዳ መንግስታዊ ስርዓትና መዋቅር መገንባት ወሳኝ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ አስገንዝበዋል፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከርና ከጎረቤት አገራት ጋር በመሰረተ ልማት በመተሳሰር የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የምንሰጠው ትምህርት ወቅቱ ከደረሰበት የቴክኖሎጂ እድገት ጋር ሊያራምድ የሚችል መሆኑን እየፈተሹና እያረጋገጡ መሄድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በመድረኩ “ትናንንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል ርዕስ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶች ዙሪያ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
“ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል ርዕስ ባለፉት ሰባት ዓመታት የለውጥ ስኬቶች ዙሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች ውይይት አካሂደዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ውይይቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ዘርፉ የአገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እድገት መሰረት በመሆኑ በቁጭትና በእልህ በመስራት የሚፈለገው ለውጥ እንዲመጣ መረባረብ ይገባል፡፡
በአገሪቱ ባለፉት ሰባት አመታት በለውጥ ጊዜ የሚጠበቁ በርካታ ተግዳሮቶች የገጠሙና አሁንም ያለተሻገርናቸው ፈተናዎች ቢኖሩም የትምህርት ዘርፉን ጨምሮ በየዘርፉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን አስረድተዋል፡፡
የለውጡ ጊዜ ማህበራዊ ሚዲያ ቀውስ የነገሰበት ፣ በዓለማችን አዲስ ስርዓት እተወለደ ያለበትና ልዩ ልዩ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች የተዛቡበት እና አስቸጋሪ ወቅት መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
በመሆኑም ችግሮችና ፈተናዎችን በጽናት በመቋቋም በቁጭት መስራትና አገሪቱንም ከእርዳታ ጠባቂነትና ከኋላ ቀርነት ማላቀቅና የህዝቦቿን ክብርና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ዘላቂ ሰላምና ዴሞክራሲን ለማስፈን እና ከአድልዎ የጸዳ መንግስታዊ ስርዓትና መዋቅር መገንባት ወሳኝ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ አስገንዝበዋል፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከርና ከጎረቤት አገራት ጋር በመሰረተ ልማት በመተሳሰር የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የምንሰጠው ትምህርት ወቅቱ ከደረሰበት የቴክኖሎጂ እድገት ጋር ሊያራምድ የሚችል መሆኑን እየፈተሹና እያረጋገጡ መሄድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
በመድረኩ “ትናንንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል ርዕስ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተመዘገቡ የለውጥ ስኬቶች ዙሪያ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
Apr 02, 2025 98
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሰን አርካዲዮ ሜኔሴስ ኮፕቴን በጽ/ ቤታቸው በመቀበል ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ሁለቱ አገራት በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚችሉባቸውን ጉዳዮች አንስተው ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኮሎምቢያ አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በማነጋገራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አንስተውላቸዋል።
በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በሙዚቃና ባህል ልውውጥ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች በትብብር መስራት እንደሚቻልም አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሰን አርካዲዮ ሜኔሴስ ኮፕቴ በበኩላቸው ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ መክፈቷን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ተናግረዋል።
አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ነጻ የትምህርት እድልና የባለሙያ ልውውጥ፣ በከፍተኛ ትምህርት የሰላም ግንባታ እንዲሁም በሙዚቃና ባህል ልምድ ልውውጥ በማድረግ ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።
ሁለቱ አካላት በቀጣይ በሚኖራቸው ግንኙነቶች በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ትብብሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሰን አርካዲዮ ሜኔሴስ ኮፕቴን በጽ/ ቤታቸው በመቀበል ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ሁለቱ አገራት በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚችሉባቸውን ጉዳዮች አንስተው ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኮሎምቢያ አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በማነጋገራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮችን ለአምባሳደሩ አንስተውላቸዋል።
በተለይም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በሙዚቃና ባህል ልውውጥ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች በትብብር መስራት እንደሚቻልም አብራርተዋል።
በኢትዮጵያ የኮሎምቢያ አምባሳደር ዬሰን አርካዲዮ ሜኔሴስ ኮፕቴ በበኩላቸው ኮሎምቢያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ መክፈቷን ገልጸው በትምህርቱ ዘርፍም ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ተናግረዋል።
አክለውም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ነጻ የትምህርት እድልና የባለሙያ ልውውጥ፣ በከፍተኛ ትምህርት የሰላም ግንባታ እንዲሁም በሙዚቃና ባህል ልምድ ልውውጥ በማድረግ ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉም አንስተዋል።
ሁለቱ አካላት በቀጣይ በሚኖራቸው ግንኙነቶች በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ትብብሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
Apr 01, 2025 82
የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በ2017 ዓ.ም ሊተገበሩ በታቀዱ የቁልፍ አፈጻጸም አመላካች ተግባራት እቅድ ላይ ከዘርፉ መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር የመግባቢያ ስምምነት ውል ተፈራረሙ፤

የከፍትኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ውሉን የተፈራረሙት መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች የአስተዳደርና መሰረተ ልማት፣የአካዳሚክ ጉዳዮች፣የምርምርና ማህበተሰብ ጉድኝት እና የኣይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች ናቸው፡፡
የተፈረመው ውል ሀላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ተመላክቷል።
የመግባቢያ ስምምነት ውል መፈራረሙ ውጤት የሚያስመዘግቡ ሥራ አስፋጻሚዎች የበለጠ የሚበረታቱበት፣ ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት ሥርዓትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሆነም ተገልጿል።
የመግባቢያ ስምምነቱ ውል ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ሥርዓት እንዲኖርና ስራ አስፈጻሚዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ተመላክቷል።
በመሆኑም አራቱም የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች በገቡት የመግባቢያ ስምምነት ውል መሠረት ስራዎቻቸውን ወደ ስራ ክፍሎች (ዴስኮች) በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ማስመዝገብ አንደሚጠበቅባቸው ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
ከወራት በፊት ትምህርት ሚኒስቴር ተመሳሳይ የመግባቢያ ስምምነት ውል ከ47 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መፈራረሙ የሚታወስ ሲሆን የትምህርት ሚኒስቴርን በመወከል የተፈራረሙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ሲሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል የተፈራረሙት የየዩኒቨርስቲዎቹ የአስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች መሆናቸው ይታወሳል።
የከፍትኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ውሉን የተፈራረሙት መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች የአስተዳደርና መሰረተ ልማት፣የአካዳሚክ ጉዳዮች፣የምርምርና ማህበተሰብ ጉድኝት እና የኣይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች ናቸው፡፡
የተፈረመው ውል ሀላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ተመላክቷል።
የመግባቢያ ስምምነት ውል መፈራረሙ ውጤት የሚያስመዘግቡ ሥራ አስፋጻሚዎች የበለጠ የሚበረታቱበት፣ ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት ሥርዓትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሆነም ተገልጿል።
የመግባቢያ ስምምነቱ ውል ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ሥርዓት እንዲኖርና ስራ አስፈጻሚዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ተመላክቷል።
በመሆኑም አራቱም የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች በገቡት የመግባቢያ ስምምነት ውል መሠረት ስራዎቻቸውን ወደ ስራ ክፍሎች (ዴስኮች) በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ማስመዝገብ አንደሚጠበቅባቸው ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።
ከወራት በፊት ትምህርት ሚኒስቴር ተመሳሳይ የመግባቢያ ስምምነት ውል ከ47 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መፈራረሙ የሚታወስ ሲሆን የትምህርት ሚኒስቴርን በመወከል የተፈራረሙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ሲሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል የተፈራረሙት የየዩኒቨርስቲዎቹ የአስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች መሆናቸው ይታወሳል።
Mar 31, 2025 117
የሀገር ውስጥ ዜና

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፍልሰት ዙሪያ በሳይንሳዊ ምርምሮች የተደገፉ ስራዎችን በማቅረብ ችግሩ እንዲቀረፍ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ።

ትምህርት ሚኒስቴር ዴዚም /Dezim / እና ሶሊሲቲ/ Soli*City/ ከተባሉ ሁለት ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡።
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በስምምነቱ ወቅት እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስደተኝነና ፍልሰት ዙሪያ ሳይንሳዊ ምርምሮችን በማድረግ ለፖሊሲ ግብኣት የሚሆኑ ሀሳቦችን ሊያመነጩ ይገባል፡።
ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርስቲዎች ጋር በቅርቡ ከተፈራረማቸው KPI / ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች/ ውስጥ አንዱ ዩኒቨርስቲዎች እንደሚገኙበት ተጨባጭ ሁኔታ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ሕገ-ወጥ ፍልሰትን በመከላከል ማህበራዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደሚገኝበት ጠቁመዋል፡፡
በተለይም ችግሩ በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መንግስት ችግሩን ለመቀነስ የሚያካሂደውን የፖሊሲ እርምጃ ለመደፍና ወደፊት ለማራመድ ጥልቅ ምርምር ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡
ዴዚል እና ሶሊሲቲ ከተባሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት መሰረት የሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ ተቋማቱ የተሻለ ምርምር ለመስራት እድል እንደሚፈጥርላቸውም ክቡር ሚኒስተር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ተጠባባቂ መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው የፍልሰተኝነትና ስደተኝንነት ችግሮች በምርምር ከመፍታት አንጻር ሰፊ ክፍተት መኖሩን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ራሳቸውን በመፈተሽ በምርምር የተደገፉ ተጽዕኖ ፈጣሪ መረጃዎችን ማመንጨት፣ ወደሌሎች ተቋማት ማስፋትና በተጠያቂነትና በኃላፊነት ችግሩን በጋራ ለመፍታት መስራት እንደሚገባቸውም ዶ/ር ሰራዊት ጨምረው ገልጸዋል፡፡፡
ሶሊሲቲን በመወከል የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት ፕሮፌሰር ሃራልድ ባውደር በበኩላቸው ትብብሩ በአፍሪካ ቀንድ በኩል የሚደረገውን ፍልሰት በመረዳት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ለማውጣትና ለችግር የተጋለጡ ስደተኖችንና ፍልሰተኖችን ለመርዳት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡።
የጀርመን የውህደት እና የፍልሰት ጥናት ማእከል (DeZIM) ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ኖአ ኬ ሃ በበኩላቸው ስምምነቱ ተቋማቸው በፍልሰተኞችና ስደተኞች ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴርና ከዩኒቨርሲቲ የምርምር ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት እንደሚያስችለው ተናግረዋል፡።
በፊርማ ስምምነቱ ወቅት በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሰባት ዩኒቨርስቲ የምርምር ምክትል ፕሬዚዳንቶች ፣ የፍትህ ሚኒስቴርና ከሌሎችም የተውጣጡ ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ዴዚም /Dezim / እና ሶሊሲቲ/ Soli*City/ ከተባሉ ሁለት ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡።
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በስምምነቱ ወቅት እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በስደተኝነና ፍልሰት ዙሪያ ሳይንሳዊ ምርምሮችን በማድረግ ለፖሊሲ ግብኣት የሚሆኑ ሀሳቦችን ሊያመነጩ ይገባል፡።
ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርስቲዎች ጋር በቅርቡ ከተፈራረማቸው KPI / ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች/ ውስጥ አንዱ ዩኒቨርስቲዎች እንደሚገኙበት ተጨባጭ ሁኔታ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ሕገ-ወጥ ፍልሰትን በመከላከል ማህበራዊ ኃላፊነትን መወጣት እንደሚገኝበት ጠቁመዋል፡፡
በተለይም ችግሩ በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መንግስት ችግሩን ለመቀነስ የሚያካሂደውን የፖሊሲ እርምጃ ለመደፍና ወደፊት ለማራመድ ጥልቅ ምርምር ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡
ዴዚል እና ሶሊሲቲ ከተባሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት መሰረት የሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ ተቋማቱ የተሻለ ምርምር ለመስራት እድል እንደሚፈጥርላቸውም ክቡር ሚኒስተር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ተጠባባቂ መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው የፍልሰተኝነትና ስደተኝንነት ችግሮች በምርምር ከመፍታት አንጻር ሰፊ ክፍተት መኖሩን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ራሳቸውን በመፈተሽ በምርምር የተደገፉ ተጽዕኖ ፈጣሪ መረጃዎችን ማመንጨት፣ ወደሌሎች ተቋማት ማስፋትና በተጠያቂነትና በኃላፊነት ችግሩን በጋራ ለመፍታት መስራት እንደሚገባቸውም ዶ/ር ሰራዊት ጨምረው ገልጸዋል፡፡፡
ሶሊሲቲን በመወከል የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት ፕሮፌሰር ሃራልድ ባውደር በበኩላቸው ትብብሩ በአፍሪካ ቀንድ በኩል የሚደረገውን ፍልሰት በመረዳት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ ለማውጣትና ለችግር የተጋለጡ ስደተኖችንና ፍልሰተኖችን ለመርዳት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡።
የጀርመን የውህደት እና የፍልሰት ጥናት ማእከል (DeZIM) ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ኖአ ኬ ሃ በበኩላቸው ስምምነቱ ተቋማቸው በፍልሰተኞችና ስደተኞች ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴርና ከዩኒቨርሲቲ የምርምር ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት እንደሚያስችለው ተናግረዋል፡።
በፊርማ ስምምነቱ ወቅት በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሰባት ዩኒቨርስቲ የምርምር ምክትል ፕሬዚዳንቶች ፣ የፍትህ ሚኒስቴርና ከሌሎችም የተውጣጡ ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።
Mar 29, 2025 88
የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ እና ፊላንድ በትምህርቱ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚችሉበት ዙሪያ ተወያዩ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የላቲን አሜሪካ ጉዳዮች ኃላፊ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ዘርፍ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ ያሉ ዋና ዋና ተግባራትን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተውለቸዋል።
በተለይም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በዚህም ማናቸውም የሚደረጉ ድጋፎች በመነጋገር ካለምንም የሀብት መባከን በትክክል ህፃናት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ እንዲውሉ ማድረግ እንደሚገባም አፅንኦት ሰጥተዋል
የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም የአካቶ ትምህርት ማዕከላትን በማስፋፋት ረገድ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
አሁንም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በምንሰራቸው የለውጥ ተግባራት የበለጠ ድጋፍ እንፈልጋለን ብለዋል።
በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የላቲን አሜሪካ ጉዳዮች ኃላፊ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን በበኩላቸው በትምህርቱ ዘርፍ ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር በርካታ ተግባራትን ማከናወኗን ጠቅሰዋል።
ይህንን በማጠናከር በትምህርቱ ዘርፍ ዘርፈ ብዙ ትብብሮችን ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት በትምህርቱ ዘርፍ በርካታ ትብብር የሚያደርጉባቸው ጉዳዮች እንዳሉ የተወያዩ ሲሆን ማናቸውም የሚደረጉ ድጋፎች በሚኒስቴሩ በተለዩ የቅድሚያ ቅድሚያ በተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ እንዲሆንም ተስማምተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የላቲን አሜሪካ ጉዳዮች ኃላፊ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር በትምህርቱ ዘርፍ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ዘርፍ የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ ያሉ ዋና ዋና ተግባራትን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተውለቸዋል።
በተለይም ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በዚህም ማናቸውም የሚደረጉ ድጋፎች በመነጋገር ካለምንም የሀብት መባከን በትክክል ህፃናት ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ እንዲውሉ ማድረግ እንደሚገባም አፅንኦት ሰጥተዋል
የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም የአካቶ ትምህርት ማዕከላትን በማስፋፋት ረገድ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
አሁንም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በምንሰራቸው የለውጥ ተግባራት የበለጠ ድጋፍ እንፈልጋለን ብለዋል።
በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ መካከለኛው ምስራቅ እና የላቲን አሜሪካ ጉዳዮች ኃላፊ አምባሳደር ሄሌና አይራክሲነን በበኩላቸው በትምህርቱ ዘርፍ ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር በርካታ ተግባራትን ማከናወኗን ጠቅሰዋል።
ይህንን በማጠናከር በትምህርቱ ዘርፍ ዘርፈ ብዙ ትብብሮችን ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት በትምህርቱ ዘርፍ በርካታ ትብብር የሚያደርጉባቸው ጉዳዮች እንዳሉ የተወያዩ ሲሆን ማናቸውም የሚደረጉ ድጋፎች በሚኒስቴሩ በተለዩ የቅድሚያ ቅድሚያ በተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ እንዲሆንም ተስማምተዋል።
Mar 22, 2025 529

ሚኒስትሮቻችን

MINISTER

ክቡር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

STATE MINISTER

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት

STATE MINISTER

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ