እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ 5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደርስ (5 million Ethiopian Coders) የተሰኘ ስልጠና አመቻችቷል።

መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ “5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ” የተሰኘ አዲስ የስልጠና እድል አመቻችቷል። ይህ ኢኒሼቲቭ ከአይሲቲ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ኮርሶች ጥራቱና በጥልቅ ይዘቶች በሚታወቀው በኦዳሲቲ ፕላትፎርም (Udacity Platform) የፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስና ሌሎችም ከአይሲቲ ጋር የተገናኙ ኮርሶችን ከክፍያ ነፃ ማግኘት የሚያስችል ነው።
ተማሪዎች እና መምህራን ያለምንም ወጪ በእነዚህ ኮርሶች በመመዝገብ ይህንን ልዩ የስልጠና እድል መጠቀም የሚችሉ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ውስጥ በመሳተፍና ችሎታቸውን በማጎልበት በአለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ ተወዳዳሪ መሆን ይችላሉ።
በዚህ ስልጠና ተመዝግበውና የትምህርት ይዘቶቹን ተምረው ያጠናቀቁ ተሳታፊዎች በአለም አቀፍ ድርጅቶች እውቅና ያለው እና የስራ እድልን በእጅጉ ሊያሳድግ ከሚችለው Udacity የምስክር ወረቀት ያገኛሉ።
ትምህርት ሚኒስቴር በስልጠናው እንዴት መመዝገብና መሳተፍ እንደሚቻል የሚያሳዩ መመሪያዎችን በጽሁፍና በቪዲዮ አዘጋጅቷል። ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎችና መምህራን ይሄንን በበዙ ክፍያ ይሰጥ የነበረን ስልጠና መመሪያውን ተከትሎ ብቻ በመመዝገብ በነጻ መሰልጠን ትችላላችሁ።
የመመሪያውን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/-zSmhhD5qE4 ላይ በመግባት መመልከት የምትችሉ ሲሆን በምስል የተደገፈውን መመሪያም ከዚህ ፖስት ጋር አጋርተናል።
ይሄንን ጠቃሚና ነጻ የስልጠና እድል ፍላጎቱ ላላቸውና የትምህርት ዝግጅታቸው ከዚህ ስልጠና ጋር ለሚገናኝ ጓደኞቻችሁ፣ ወዳጅ ፣ ቤተሰባችሁ እንዲሁም ተማሪዎችና መምህራን በማጋራት ተጨቃሚ እንዲሆኑ አድርጉ።
መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ “5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ” የተሰኘ አዲስ የስልጠና እድል አመቻችቷል። ይህ ኢኒሼቲቭ ከአይሲቲ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ኮርሶች ጥራቱና በጥልቅ ይዘቶች በሚታወቀው በኦዳሲቲ ፕላትፎርም (Udacity Platform) የፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስና ሌሎችም ከአይሲቲ ጋር የተገናኙ ኮርሶችን ከክፍያ ነፃ ማግኘት የሚያስችል ነው።
ተማሪዎች እና መምህራን ያለምንም ወጪ በእነዚህ ኮርሶች በመመዝገብ ይህንን ልዩ የስልጠና እድል መጠቀም የሚችሉ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ውስጥ በመሳተፍና ችሎታቸውን በማጎልበት በአለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ ተወዳዳሪ መሆን ይችላሉ።
በዚህ ስልጠና ተመዝግበውና የትምህርት ይዘቶቹን ተምረው ያጠናቀቁ ተሳታፊዎች በአለም አቀፍ ድርጅቶች እውቅና ያለው እና የስራ እድልን በእጅጉ ሊያሳድግ ከሚችለው Udacity የምስክር ወረቀት ያገኛሉ።
ትምህርት ሚኒስቴር በስልጠናው እንዴት መመዝገብና መሳተፍ እንደሚቻል የሚያሳዩ መመሪያዎችን በጽሁፍና በቪዲዮ አዘጋጅቷል። ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎችና መምህራን ይሄንን በበዙ ክፍያ ይሰጥ የነበረን ስልጠና መመሪያውን ተከትሎ ብቻ በመመዝገብ በነጻ መሰልጠን ትችላላችሁ።
የመመሪያውን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/-zSmhhD5qE4 ላይ በመግባት መመልከት የምትችሉ ሲሆን በምስል የተደገፈውን መመሪያም ከዚህ ፖስት ጋር አጋርተናል።
ይሄንን ጠቃሚና ነጻ የስልጠና እድል ፍላጎቱ ላላቸውና የትምህርት ዝግጅታቸው ከዚህ ስልጠና ጋር ለሚገናኝ ጓደኞቻችሁ፣ ወዳጅ ፣ ቤተሰባችሁ እንዲሁም ተማሪዎችና መምህራን በማጋራት ተጨቃሚ እንዲሆኑ አድርጉ።
Jul 26, 2024 129
የሀገር ውስጥ ዜና

የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና

የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና

የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና

Jul 23, 2024 625
የሀገር ውስጥ ዜና

የ2016 ዓ. ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና በሠላም መጠናቀቁ ተገለፀ።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና በሠላም መጠናቀቁን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በመላ ሀገሪቱ በወረቀትና በኦላይን ሲሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሰላም መጠናቀቁን ገልፀዋል።
በዚህም ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 701,749 ተማሪዎች ውስጥ 684,372 ተማሪዎች ፈተናቸውን መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ ፈተናው በሰላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጻኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። ሙሉ መግለጫውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ። rb.gy/u17yql
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና በሠላም መጠናቀቁን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በመላ ሀገሪቱ በወረቀትና በኦላይን ሲሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በሰላም መጠናቀቁን ገልፀዋል።
በዚህም ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 701,749 ተማሪዎች ውስጥ 684,372 ተማሪዎች ፈተናቸውን መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ ፈተናው በሰላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጻኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። ሙሉ መግለጫውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ። rb.gy/u17yql
Jul 19, 2024 619
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞችን አበረታቱ።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ በአብርሆት ቤተመጻህፍትና በመነን ትምህርት ቤት መፈተኛ ጣቢያዎች በመገኘት የፈተና እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል። ተፈታኝ ተማሪዎችንም አበረታተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ከሐምሌ 03 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን በመፈተን ማስጀምሩ ይታወሳል። ይሄው አገር አቀፍ ፈተና ሁለተኛውን ዙር ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም በተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የቀጠለ ሲሆን በትግራይ ክልል በአሮጌው ካሪኩለም የሚፈተኑ ተማሪዎች በነገው እለት ሲያጠናቀቁ የሌሎች ክልሎች ተፈታኞች በዛሬው እለት የሚጨርሱ ይሆናል።
ክብርት ወ/ሮ አየለች ጉብኝቱን ባደረጉት ወቅት ለፈተናው የተደረገው ዘርፈብዙ ዝግጅትና ውጤት የተቋማት ትብብር የፈጠረው ውጤታማነት መሆኑን ገልጸዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ በአብርሆት ቤተመጻህፍትና በመነን ትምህርት ቤት መፈተኛ ጣቢያዎች በመገኘት የፈተና እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል። ተፈታኝ ተማሪዎችንም አበረታተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ከሐምሌ 03 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን በመፈተን ማስጀምሩ ይታወሳል። ይሄው አገር አቀፍ ፈተና ሁለተኛውን ዙር ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም በተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የቀጠለ ሲሆን በትግራይ ክልል በአሮጌው ካሪኩለም የሚፈተኑ ተማሪዎች በነገው እለት ሲያጠናቀቁ የሌሎች ክልሎች ተፈታኞች በዛሬው እለት የሚጨርሱ ይሆናል።
ክብርት ወ/ሮ አየለች ጉብኝቱን ባደረጉት ወቅት ለፈተናው የተደረገው ዘርፈብዙ ዝግጅትና ውጤት የተቋማት ትብብር የፈጠረው ውጤታማነት መሆኑን ገልጸዋል።
Jul 18, 2024 329
የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር ውይይት አደረጉ

የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር በትምህርት ዘርፉ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል። በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ከሀገራቸው የትምህርት ሚኒስቴር፣ ትምህርትን ከሚደግፉ የልማት ድርጅቶች ጋር በመተባበር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የኢትዮጵያን የትምህርት ሪፎርም ለመደገፍ በተለይም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የት/ቤቶችን መስፋፋትና እድሳት፣ የት/ቤት ምገባ ለማገዝና እና የተለያዩ የመምህራን ክህሎት ማሻሻያ ስልጠናዎች ለመስጠት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት በዩኒቨርስቲዎች መካከል በሚደረግ ትብብር፣ በነጻ ትምህርት እድል፣ በጋራ የምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር በትምህርት ዘርፉ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል። በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ከሀገራቸው የትምህርት ሚኒስቴር፣ ትምህርትን ከሚደግፉ የልማት ድርጅቶች ጋር በመተባበር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የኢትዮጵያን የትምህርት ሪፎርም ለመደገፍ በተለይም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የት/ቤቶችን መስፋፋትና እድሳት፣ የት/ቤት ምገባ ለማገዝና እና የተለያዩ የመምህራን ክህሎት ማሻሻያ ስልጠናዎች ለመስጠት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት በዩኒቨርስቲዎች መካከል በሚደረግ ትብብር፣ በነጻ ትምህርት እድል፣ በጋራ የምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
Jul 18, 2024 244
የሀገር ውስጥ ዜና

ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈታናን አስጀመሩ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በአብርሆት ቤተ-መጽሃፍት በመገኘት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ብሄራዊ ፈተናን አስጀምረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በዚህ ዓመት እየተተገበረ ያለው የወረቀትና የኦን ላይን ፈተና (hybrid exam) መሆኑን አመልክተዋል። ለወደፊቱ ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን መፈተን ሲቻል የበለጠ ፈተናውን ከስርቆትና ከመኮራረጅ ከመታደጉም በላይ ለትምህርት ጥራት የበኩሉን ድርሻ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ፈተናውን ለማስተዳደር፣ ለቁጥጥር፣ ለህትመት፣ ለማጓጓዝ፣ ለሴኩዩሪቲ እና መሰል ወጭዎችን ለመቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በመጨረሻም የፈተናውን ድባብ ለማበላሸት ሀሰተኛ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ስለሚንሸራሸሩ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ አሳስበው ተማሪዎችም ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲሰሩ መክረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በአብርሆት ቤተ-መጽሃፍት በመገኘት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ብሄራዊ ፈተናን አስጀምረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በዚህ ዓመት እየተተገበረ ያለው የወረቀትና የኦን ላይን ፈተና (hybrid exam) መሆኑን አመልክተዋል። ለወደፊቱ ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን መፈተን ሲቻል የበለጠ ፈተናውን ከስርቆትና ከመኮራረጅ ከመታደጉም በላይ ለትምህርት ጥራት የበኩሉን ድርሻ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ፈተናውን ለማስተዳደር፣ ለቁጥጥር፣ ለህትመት፣ ለማጓጓዝ፣ ለሴኩዩሪቲ እና መሰል ወጭዎችን ለመቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በመጨረሻም የፈተናውን ድባብ ለማበላሸት ሀሰተኛ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ስለሚንሸራሸሩ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ አሳስበው ተማሪዎችም ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲሰሩ መክረዋል።
Jul 10, 2024 927

ሚኒስትሮቻችን

MINISTER

ክቡር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

STATE MINISTER

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት

STATE MINISTER

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ