እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ ከቻይና የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከቻይና የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የቻይና የቋንቋ ትምህርትና ትብብር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር Yu Yunfeng ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ የቻይና ስትራቴጂክ አጋር ናት ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ በኢንቨስትመንት ረገድ ከምታደርገው ትብብር በተጨማሪ የቻይና ቋንቋ ትምህርት በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን በሌሎች የትምህርት ተቋማት በማስፋፋት የቻይና ቋንቋን ማስተማር እንደሚፈልጉ ገልጸውላቸዋል።
ይህም ዜጎች በርካታ ቋንቋዎችን እንዲያውቁ ከማድረጉም ባሻገር የህዝብ ለህዝብ ትብብርን የበለጠ በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ቻይና ለረጅም ጊዜ የቆየ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸውና የብሪክስ አባል ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው አሁን ባለው የኢትዮጵያና የቻይና ግንኙነት የቻይና ቋንቋ በኢትዮጵያ የትምህርት ተቋማት ቢሰጥ ለዜጎች ጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል።
በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ የቋንቋ ትምህርትን በተመለከተ በግልጽ የተቀመጡ ጉዳዮችን ለልዑካን ቡድኑ ያብራሩት ክቡር ሚኒስትሩ በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረውን የቻይና ቋንቋ ትምህርት በሌሎች የትምህርት ተቋማት ለማስፋፋት ፍላጎቶች እንዳሉና አተገባበሩን በተመለከተ ውይይት ማድረግ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
አያይዘውም በዚህ ዓመት የመማር ማስተማር በሚጀመርባቸው አምስት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቻይና ቋንቋን ለማስተማር በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ፍላጎት እንዳለ በማንሳት የቻይና ቋንቋ መምህራንን እንዲመደቡ የልዑካን ቡድኑን ጠይቀዋል።
ሁለቱ አካላት በውይይታቸውም በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚሰጠውን የቻይና ቋንቋ ትምህርትን በተመለከተ የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ መዘጋጀት እንዳለበት እና በሌሎች የትምህርት ተቋማት ለመተግበር እንዲቻል የሥርዓተ ትምህርት፣ የመጽሃፍት እና የመምህራን አቅርቦትን በተመለከተ አስቀድሞ መወያየት እንደሚገባ አንስተዋል።
በመጨረሻም በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ስምምነት የተደረሰባቸውን ጉዳዮች ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ዝርዝር የስምምነት ሰነድ ከሁለቱ አካላት በተውጣጣ ኮሚቴ እንዲዘጋጅ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከቻይና የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የቻይና የቋንቋ ትምህርትና ትብብር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር Yu Yunfeng ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ የቻይና ስትራቴጂክ አጋር ናት ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ በኢንቨስትመንት ረገድ ከምታደርገው ትብብር በተጨማሪ የቻይና ቋንቋ ትምህርት በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰው ይህንን በሌሎች የትምህርት ተቋማት በማስፋፋት የቻይና ቋንቋን ማስተማር እንደሚፈልጉ ገልጸውላቸዋል።
ይህም ዜጎች በርካታ ቋንቋዎችን እንዲያውቁ ከማድረጉም ባሻገር የህዝብ ለህዝብ ትብብርን የበለጠ በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው ኢትዮጵያና ቻይና ለረጅም ጊዜ የቆየ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸውና የብሪክስ አባል ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው አሁን ባለው የኢትዮጵያና የቻይና ግንኙነት የቻይና ቋንቋ በኢትዮጵያ የትምህርት ተቋማት ቢሰጥ ለዜጎች ጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል።
በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ የቋንቋ ትምህርትን በተመለከተ በግልጽ የተቀመጡ ጉዳዮችን ለልዑካን ቡድኑ ያብራሩት ክቡር ሚኒስትሩ በተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረውን የቻይና ቋንቋ ትምህርት በሌሎች የትምህርት ተቋማት ለማስፋፋት ፍላጎቶች እንዳሉና አተገባበሩን በተመለከተ ውይይት ማድረግ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
አያይዘውም በዚህ ዓመት የመማር ማስተማር በሚጀመርባቸው አምስት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቻይና ቋንቋን ለማስተማር በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ፍላጎት እንዳለ በማንሳት የቻይና ቋንቋ መምህራንን እንዲመደቡ የልዑካን ቡድኑን ጠይቀዋል።
ሁለቱ አካላት በውይይታቸውም በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚሰጠውን የቻይና ቋንቋ ትምህርትን በተመለከተ የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ መዘጋጀት እንዳለበት እና በሌሎች የትምህርት ተቋማት ለመተግበር እንዲቻል የሥርዓተ ትምህርት፣ የመጽሃፍት እና የመምህራን አቅርቦትን በተመለከተ አስቀድሞ መወያየት እንደሚገባ አንስተዋል።
በመጨረሻም በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ስምምነት የተደረሰባቸውን ጉዳዮች ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ዝርዝር የስምምነት ሰነድ ከሁለቱ አካላት በተውጣጣ ኮሚቴ እንዲዘጋጅ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
Dec 05, 2025 140
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ ከደቡብ አፍሪካ የመጡ የልዑካን ቡድን አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይትም University of South Africa (UNISA) በኢትዮጵያ እንዴት በትብብር መስራት እንደሚችል ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የUnisa’s Principal and Vice-Chancellor Prof Puleng LenkaBula ፤ UNISA ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ከ2006 ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ መስክ በርካታ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ሲያስመርቅ መቆየቱን ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከፍተኛ ችግር የነበረበትና በከፍተኛ ትምህርት ዜጎች ዲግሪ በገንዘብ የሚገዙበት ጭምር የነበረ በመሆኑ፤
ይህንን ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የትምህርት ጥራትን ሊያረጋግጡ እንዲሁም ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ መሆኑና በዚህም ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ዓለም በፈጣን እድገት ላይ ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ በጣም ውስብስብ እየሆነች መጥታለች ያሉት ሚኒስትሩ UNISA ከ20 ዓመት በፊት በጀመረው ስምምነትና ፕሮግራም መሰረት አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፍላጎትና የኢኮኖሚ እድገት ሊቀጥል የማይችል በመሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያስችል መልኩ መታየት እንዳለበት አስገንዝበው በአፍሪካ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮች ይህንን መሰረት ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ሥራዎችም ሀገራችን ለያዘቻቸው የልማት እቅዶች መሳካት የሚያስፈልግ የሰው ሃይል ልማትን በሚያግዙ የትምህርት መስኮች እንደ ማዕድን፣ ፔትሮ ኬሚካል፣ አግሮ ኢንደስትሪ የመሳሰሉት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን ይገባቸዋልም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው UNISA በሀገራችን ላለፉት 20 ዓመታት ሲሰራ መቆየቱ ቢታወቅም፣ በቀጣይ የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲስ ውይይት ማድረግ ይቻላል ብለዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየትኞቹ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት እንደሚቻል እንዲለዩና ለቀጣይ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲቀርቡ ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የUNISA ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አመራሮች ተግኝተዋል።
በዚሁ ጊዜ የልዑካን ቡድኑን የመሩት የUnisa’s Principal and Vice-Chancellor Prof Puleng LenkaBula ፤ UNISA ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ከ2006 ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር እና በቴክኖሎጂ መስክ በርካታ ተማሪዎችንና የመንግስት ሰራተኞችን ሲያስመርቅ መቆየቱን ለክቡር ሚኒስትሩ አብራርተውላቸዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከፍተኛ ችግር የነበረበትና በከፍተኛ ትምህርት ዜጎች ዲግሪ በገንዘብ የሚገዙበት ጭምር የነበረ በመሆኑ፤
ይህንን ለማስተካከል በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የትምህርት ጥራትን ሊያረጋግጡ እንዲሁም ብቃት ያላቸው፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች እየተተገበሩ መሆኑና በዚህም ለውጦች እየተመዘገቡ መምጣታቸውን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ዓለም በፈጣን እድገት ላይ ስትሆን በሌላ በኩል ደግሞ በጣም ውስብስብ እየሆነች መጥታለች ያሉት ሚኒስትሩ UNISA ከ20 ዓመት በፊት በጀመረው ስምምነትና ፕሮግራም መሰረት አሁን ባለው የኢትዮጵያ ፍላጎትና የኢኮኖሚ እድገት ሊቀጥል የማይችል በመሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሚያስችል መልኩ መታየት እንዳለበት አስገንዝበው በአፍሪካ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮች ይህንን መሰረት ያደረጉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረጉ የጋራ ሥራዎችም ሀገራችን ለያዘቻቸው የልማት እቅዶች መሳካት የሚያስፈልግ የሰው ሃይል ልማትን በሚያግዙ የትምህርት መስኮች እንደ ማዕድን፣ ፔትሮ ኬሚካል፣ አግሮ ኢንደስትሪ የመሳሰሉት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን ይገባቸዋልም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው UNISA በሀገራችን ላለፉት 20 ዓመታት ሲሰራ መቆየቱ ቢታወቅም፣ በቀጣይ የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲስ ውይይት ማድረግ ይቻላል ብለዋል።
ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በየትኞቹ ጉዳዮች በትብብር ለመስራት እንደሚቻል እንዲለዩና ለቀጣይ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮች እንዲቀርቡ ተስማምተዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የUNISA ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ አመራሮች ተግኝተዋል።
Nov 29, 2025 207
የሀገር ውስጥ ዜና

እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስ በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም እቀፍ ህጻናት አድን ድርጅት ጋር በመተባበር” በኢትዮጵያ የፍልሰት ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሲቪክ ማህባራት፣መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ-ጥናት ተካሂዷል፡፡
በአውደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስቴር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስም ሆነ በሚገባ ለማስተዳደር በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻና አጋር አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
አውደ-ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች የጋራ ትብብርና ቅንጅት በሚሰሩ ምርምሮች የሚለዩ የህግ ማዕቀፎችና የአተገባበር ክፍተቶች አግባብነት ባላቸው ተቋማት ተወስደው ለአስፈጻሚዎች ውሳኔና ለፋጻሚዎች ትግበራ ማሻሻያነት የሚውሉበት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮፌሰር ክንደያ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለፍልሰት በተሰጠው ሀገራዊ ትኩረት የፍልሰት ምርምር ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት የምርምር ስትራጂዎች መካከል አንዱ እንዲሆን ከመደረጉ በተጨማሪ ፍልሰት እንደ አንድ ዋነኛ የማህበረሰብ አጀንዳ ተወሶዶ እንዲሰራበት መደረጉንም ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት የፕሮግራም ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ድርጅታቸው ለብሄራዊ ፍልሰት ምላሽ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከፍልሰት ምርምር የሚገኙ ግብዓቶች ደግሞ ፕሮግራሙ ይበልጥ በውጤታማነት እንዲፈጸም የሚያግዙ እቅዶችን ለማቀድ የሚረዱ በመሆናቸው ድርጅታቸው ምርምርን አጽዕኖት ሰጥቶ የሚደግፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት ባሉት የተለያዩ ችግሮች የተነሰ እየጨመሩ የመጡ የፍልሰት ተጋላጭነቶችንና ጉዳቶችን ለመቀንስ ቅንጅትና አስቸኳይ የጋራ ምላሾች የሚያስፈልጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር ብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብረሃም አያሌው ባለፉት ሦስት አመታት ፍልሰት ብሄራዊ የልማትና ደህንነት አጀንዳ ወደ መሆን የተሸጋገረ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህም በመሆኑ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በፍልሰት ላይ ያተኮረ የድህረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎች መክፈታቸውንና የተወሰኑት ደግሞ የፍልሰት ምርምር ማዕከላት ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀገራችን በዓለም አቀፍ፣ በአህጉርና በኢጋድ ሀገራት ደረጃ የተለያዩ የፍልሰት ስምምነቶችን ተቀብላ የህጎቿ አካል አድርጋ እየተገበረች መሆኗን ጠቅሰው ከጥቂት አመታት ወዲህ ለፍልሰት በተሰጠው ትኩረት ሀገራዊ የፍልሰት ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
በአውደ-ጥናቱ ላይ የተላያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ውጤታማነትና ለአውደ-ጥናቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር ከዓለም እቀፍ ህጻናት አድን ድርጅት ጋር በመተባበር” በኢትዮጵያ የፍልሰት ምርምርን ለማሳደግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ቃል በፍልሰት ላይ የሚሰሩ የሲቪክ ማህባራት፣መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ-ጥናት ተካሂዷል፡፡
በአውደ-ጥናቱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስቴር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የዜጎች ፍልሰት ለመቀነስም ሆነ በሚገባ ለማስተዳደር በምርምር ሥርዓት የሚደገፍ የባለድርሻና አጋር አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
አውደ-ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች የጋራ ትብብርና ቅንጅት በሚሰሩ ምርምሮች የሚለዩ የህግ ማዕቀፎችና የአተገባበር ክፍተቶች አግባብነት ባላቸው ተቋማት ተወስደው ለአስፈጻሚዎች ውሳኔና ለፋጻሚዎች ትግበራ ማሻሻያነት የሚውሉበት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል፡፡
ፕሮፌሰር ክንደያ አክለውም በአሁኑ ወቅት ለፍልሰት በተሰጠው ሀገራዊ ትኩረት የፍልሰት ምርምር ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት የምርምር ስትራጂዎች መካከል አንዱ እንዲሆን ከመደረጉ በተጨማሪ ፍልሰት እንደ አንድ ዋነኛ የማህበረሰብ አጀንዳ ተወሶዶ እንዲሰራበት መደረጉንም ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ የህጻናት አድን ድርጅት የፕሮግራም ትግበራ ዳይሬክተር አቶ አብዱረዛቅ አህመድ ድርጅታቸው ለብሄራዊ ፍልሰት ምላሽ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ከፍልሰት ምርምር የሚገኙ ግብዓቶች ደግሞ ፕሮግራሙ ይበልጥ በውጤታማነት እንዲፈጸም የሚያግዙ እቅዶችን ለማቀድ የሚረዱ በመሆናቸው ድርጅታቸው ምርምርን አጽዕኖት ሰጥቶ የሚደግፍ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም በአሁኑ ወቅት ባሉት የተለያዩ ችግሮች የተነሰ እየጨመሩ የመጡ የፍልሰት ተጋላጭነቶችንና ጉዳቶችን ለመቀንስ ቅንጅትና አስቸኳይ የጋራ ምላሾች የሚያስፈልጉ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር ብሄራዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አብረሃም አያሌው ባለፉት ሦስት አመታት ፍልሰት ብሄራዊ የልማትና ደህንነት አጀንዳ ወደ መሆን የተሸጋገረ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ይህም በመሆኑ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች በፍልሰት ላይ ያተኮረ የድህረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎች መክፈታቸውንና የተወሰኑት ደግሞ የፍልሰት ምርምር ማዕከላት ማቋቋማቸውን ገልጸዋል፡፡
ሀገራችን በዓለም አቀፍ፣ በአህጉርና በኢጋድ ሀገራት ደረጃ የተለያዩ የፍልሰት ስምምነቶችን ተቀብላ የህጎቿ አካል አድርጋ እየተገበረች መሆኗን ጠቅሰው ከጥቂት አመታት ወዲህ ለፍልሰት በተሰጠው ትኩረት ሀገራዊ የፍልሰት ረቂቅ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
በአውደ-ጥናቱ ላይ የተላያዩ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ለትብብር ጥምረቱ ሴክሬታሪያት ውጤታማነትና ለአውደ-ጥናቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
Nov 23, 2025 185
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ በሲንጋፖር አምባሳደር የተመራ የልዑካን ቡድንን ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሲንጋፖር አምባሳደርንና በሲንጋፖር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉዳይ ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን በማሻሻል ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለልኡካን ቡድኑ ገልፀዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በጀመረቻቸው አዳዲስ የልማት እቅዶች እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ቱሪዝም፣ ኒውክለር ሳይንስ እና በመሳሰሉት የትምህርት መስኮች ላይ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑን የመሩት አምባሳደር H.E Aselverjah በበኩላቸው ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ አጠናክራ በመቀጠል በቴክኖሎጂ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ፣ በሥርዓተ ትምህርትና ነጻ የትምህርት እድል በመስጠት ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
አያይዘውም በሲንጋፖር የትብብር ፕሮግራም የሰው ሃብት ልማት ፕሮጀክት እስከ አሁን 160 ሺህ በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በሲንጋፖር ዩኒቨርሲቲዎች መማራቸውና ከነዚህ ውስጥ 300 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት አብራርተዋል።
ይህንን ፕሮግራም በአሁኑ ሰዓት የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል የመስጠት ፍላጎት ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ክቡር ሚኒስትሩም የሚሰጠው የነጻ የትምህርት እድል በኢትዮጵያ በማይሰጡና አዲስ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ጠቃሚ በሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረጡ ተማሪዎችን በመላክ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሲንጋፖር አምባሳደርንና በሲንጋፖር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉዳይ ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በዚሁ ጊዜ ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን በማሻሻል ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለመስጠት እየወሰደቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለልኡካን ቡድኑ ገልፀዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ በጀመረቻቸው አዳዲስ የልማት እቅዶች እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ቱሪዝም፣ ኒውክለር ሳይንስ እና በመሳሰሉት የትምህርት መስኮች ላይ በትብብር የመስራት ፍላጎት እንዳለ አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑን የመሩት አምባሳደር H.E Aselverjah በበኩላቸው ሲንጋፖር ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትብብር የበለጠ አጠናክራ በመቀጠል በቴክኖሎጂ ልውውጥ፣ በአቅም ግንባታ፣ በሥርዓተ ትምህርትና ነጻ የትምህርት እድል በመስጠት ረገድ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
አያይዘውም በሲንጋፖር የትብብር ፕሮግራም የሰው ሃብት ልማት ፕሮጀክት እስከ አሁን 160 ሺህ በላይ የአፍሪካ ተማሪዎች በሲንጋፖር ዩኒቨርሲቲዎች መማራቸውና ከነዚህ ውስጥ 300 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት አብራርተዋል።
ይህንን ፕሮግራም በአሁኑ ሰዓት የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው የትምህርት መስኮች የነጻ የትምህርት እድል የመስጠት ፍላጎት ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ክቡር ሚኒስትሩም የሚሰጠው የነጻ የትምህርት እድል በኢትዮጵያ በማይሰጡና አዲስ ለተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ጠቃሚ በሆኑ የትምህርት መስኮች የተመረጡ ተማሪዎችን በመላክ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚደረግ መሆኑን ተናግረዋል።
Nov 22, 2025 162
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ የናይጄሪያ ቴክኒካል ድጋፍ በጎፈቃደኞች ድርጅት ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከናይጄሪያ ቴክኒክ ድጋፍ በጎፈቃደኞች ድርጅት ልዑክ ጋር በጽ/ቤታቸው ተወያይተዋል።

የሁለቱ አካላት ውይይት ናይጄሪያ ከዚህ ቀደም ለሀገራችን ስትሰጥ የነበረውና ተቋርጦ የቆየውን የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው ።

በዚሁ ጊዜ ናይጄሪያ ከኢትዮጵያጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን ያነሱት የልዑካን ቡድኑ መሪ ሀገራቸው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተዋል።

ነገር ግን ይህ የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱንና አሁን ላይ የናይጄሪያ መንግስት ይህንን በትምህርቱ ዘርፉ የሚያደርገውን የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል ፍላጎት ያለው በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማሰማራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለክቡር ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ በበኩላቸው ይህ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረገው የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ሀገራችንን የበለጠ ተጠቃሚ እንድትሆን እንደሚያስችል እምነታቸውን መሆኑ ገልጸዋል።

‎በተለይም በሀገራችን ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉትን እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ኒውክለር ሳይንስ እና ለመሳሰሉት አዳዲስ የሙያ መስኮች የናይጄሪያ ተሞክሮ አስፈላጊ መሆኑን አንስተውላቸዋል።
‎በመሆኑም በነዚህ አዳዲስ የትምህርት መስኮች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ሙሁራንን ወደ አገራችን ቢመጡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በመላክ ልምድ እንዲወስዱ ቢደርግ ጠቃሚ እንደሚሆንም ለዑካን ቡድኑ ገልጸውላቸዋል።

ለዚህም ተግባራዊነት የልዑካን ቡድኑ መሪና የትምህርት ሚኒስቴር ቴክኒካል ቡድን ከላይ በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ዝርዝር ዝግጅት በቀጣይ እንዲደርግ ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ተስማምተዋል።
የሁለቱ አካላት ውይይት ናይጄሪያ ከዚህ ቀደም ለሀገራችን ስትሰጥ የነበረውና ተቋርጦ የቆየውን የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው ።

በዚሁ ጊዜ ናይጄሪያ ከኢትዮጵያጋር የቆየ ወዳጅነት ያላት ሀገር መሆኗን ያነሱት የልዑካን ቡድኑ መሪ ሀገራቸው ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ስታደርግ መቆየቷን አንስተዋል።

ነገር ግን ይህ የበጎ ፈቃደኞች የቴክኒክ ድጋፍ በተለያየ ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱንና አሁን ላይ የናይጄሪያ መንግስት ይህንን በትምህርቱ ዘርፉ የሚያደርገውን የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ማስቀጠል ፍላጎት ያለው በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማሰማራት የሚቻልበትን ሁኔታ ለክቡር ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ በበኩላቸው ይህ በትምህርቱ ዘርፍ የሚደረገው የበጎ ፈቃደኞች ቴክኒክ ድጋፍ ሀገራችንን የበለጠ ተጠቃሚ እንድትሆን እንደሚያስችል እምነታቸውን መሆኑ ገልጸዋል።

‎በተለይም በሀገራችን ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉትን እንደ ፔትሮ ኬሚካል፣ ማዕድን ልማት፣ ኒውክለር ሳይንስ እና ለመሳሰሉት አዳዲስ የሙያ መስኮች የናይጄሪያ ተሞክሮ አስፈላጊ መሆኑን አንስተውላቸዋል።
‎በመሆኑም በነዚህ አዳዲስ የትምህርት መስኮች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ሙሁራንን ወደ አገራችን ቢመጡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ባለሙያዎችን በመላክ ልምድ እንዲወስዱ ቢደርግ ጠቃሚ እንደሚሆንም ለዑካን ቡድኑ ገልጸውላቸዋል።

ለዚህም ተግባራዊነት የልዑካን ቡድኑ መሪና የትምህርት ሚኒስቴር ቴክኒካል ቡድን ከላይ በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ዝርዝር ዝግጅት በቀጣይ እንዲደርግ ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይት ተስማምተዋል።
Nov 21, 2025 420
የሀገር ውስጥ ዜና

34ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባዔ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተጀመረ፤

'ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም'' በሚል መሪ ቃል በተጀመረው ጉባዔ የ2017 የትምህርት ልማት ዘርፍ አፈጻጸም ይገመገማል።
‎ጉባዌው በ2018 የትምህርት ዘመን እቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ለተሻለ አፈጻጸም የሚያግዙ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
‎በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገር አቀፍ ጉባዔ የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
‎በተጨማሪም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ፣የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፣የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶችና አጋሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
'ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም'' በሚል መሪ ቃል በተጀመረው ጉባዔ የ2017 የትምህርት ልማት ዘርፍ አፈጻጸም ይገመገማል።
‎ጉባዌው በ2018 የትምህርት ዘመን እቅድ ላይ ውይይት በማድረግ ለተሻለ አፈጻጸም የሚያግዙ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
‎በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ እየተካሄደ በሚገኘው ሀገር አቀፍ ጉባዔ የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
‎በተጨማሪም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ፣የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፣የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶችና አጋሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
Nov 11, 2025 554

ሚኒስትሮቻችን

ሚኒስቴር

ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

ሚኒስቴር ዴታ

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ

ሚኒስቴር ዴታ

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ

ሚኒስቴር ዴታ

ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ