News

National News

በትምህርት ሚኒስቴር፣ በውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል የ5 ሚሊዮን ፓውንድ ስምምነት ተፈረመ፤

በትምህርት ሚኒስቴር፣ በዩናይትድ ኪንግደም የውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማሻሻል የሚያስችል የሶስትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል።
በለንደን ከተማ እየተካሄደ ከሚገኘው የአለም የትምህርት ፎረም 2026 ጎን ለጎን የትምህርት ሚኒስቴር፣ በውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማጠናከርና ለማሻሻል የሚያስችል የአምስት ሚሊየን ፓውንድ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል፣ የመምህራን አቅምን ለማጎልበት እና የተማሪዎችን የቋንቋ ክህሎት ተገልጿል።
ይህ ስምምነት የአምስት ሚሊየን ፓውንድ ፕሮጀክት ሲሆን በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋን በማሻሻል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋልም ተብሏል።
በተጨማሪም ስምምነቱ በትምህርት ዘርፉ ያለውን ዓለም አቀፍ ትብብር የሚያጠናክር ሲሆን፣ ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን የቋንቋ ክህሎት እንዲያዳብሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
በትምህርት ሚኒስቴር፣ በዩናይትድ ኪንግደም የውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማሻሻል የሚያስችል የሶስትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል።
በለንደን ከተማ እየተካሄደ ከሚገኘው የአለም የትምህርት ፎረም 2026 ጎን ለጎን የትምህርት ሚኒስቴር፣ በውጭ አገራት የጋራ ሀብት ልማት ቢሮ (FCDO) እና በብሪቲሽ ካውንስል መካከል የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማጠናከርና ለማሻሻል የሚያስችል የአምስት ሚሊየን ፓውንድ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል፣ የመምህራን አቅምን ለማጎልበት እና የተማሪዎችን የቋንቋ ክህሎት ተገልጿል።
ይህ ስምምነት የአምስት ሚሊየን ፓውንድ ፕሮጀክት ሲሆን በኢትዮጵያ የእንግሊዝኛ ቋንቋን በማሻሻል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋልም ተብሏል።
በተጨማሪም ስምምነቱ በትምህርት ዘርፉ ያለውን ዓለም አቀፍ ትብብር የሚያጠናክር ሲሆን፣ ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን የቋንቋ ክህሎት እንዲያዳብሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
May 21, 2026 166
National News

በአጣዬ ከተማ በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ የተገነባ የአጣዬ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተመረቀ፤

በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ በአጣዬ ከተማ የተገነባው የአጣዬ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመማሪያ ክፍል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ያስገነባው ይህ ፕሮጀክት ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን እና ዘመናዊ መፀዳጃ ቤቶችን ያካተተ ሲሆን የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአካባቢው አስተዳደር፣ የትምህርት ዘርፍ ኃላፊዎች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
የግንባታ ፕሮጀክቱ 10 ዘመናዊ የመማሪያ ክፍሎችን ያካተተ ሲሆን፣ ለወንድና ለሴት ተማሪዎች የተለያዩ መፀዳጃ ክፍሎችን ይዟል።
ፕሮጀክቱ በአካባቢው የትምህርት ተደራሽነትን እና ምቹ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረውም ተገልጿል።
በተጨማሪም በ“ትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ የትምህርት ማህበረሰቡን፣ የቀድሞ ተማሪዎችን፣ ባለሃብቶችን መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማስተባበር በመላ ሀገሪቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ፣ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና እና የትምህርት ተቋማት መሰረተ ልማት ማሻሻያ ሥራዎች በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም አካባቢዎች ፍትሃዊና ሁሉን አቀፍ ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ በአጣዬ ከተማ የተገነባው የአጣዬ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመማሪያ ክፍል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ያስገነባው ይህ ፕሮጀክት ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን እና ዘመናዊ መፀዳጃ ቤቶችን ያካተተ ሲሆን የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአካባቢው አስተዳደር፣ የትምህርት ዘርፍ ኃላፊዎች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
የግንባታ ፕሮጀክቱ 10 ዘመናዊ የመማሪያ ክፍሎችን ያካተተ ሲሆን፣ ለወንድና ለሴት ተማሪዎች የተለያዩ መፀዳጃ ክፍሎችን ይዟል።
ፕሮጀክቱ በአካባቢው የትምህርት ተደራሽነትን እና ምቹ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረውም ተገልጿል።
በተጨማሪም በ“ትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ የትምህርት ማህበረሰቡን፣ የቀድሞ ተማሪዎችን፣ ባለሃብቶችን መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማስተባበር በመላ ሀገሪቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ፣ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና እና የትምህርት ተቋማት መሰረተ ልማት ማሻሻያ ሥራዎች በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም አካባቢዎች ፍትሃዊና ሁሉን አቀፍ ጥራት ያለው ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
May 21, 2026 135
National News

Ethiopia Shared Its Experience in Building an Equitable and Inclusive Education System at the Education World Forum

Ethiopia Shared Its Experience in Building an Equitable and Inclusive Education System at the Education World Forum
Taking place in London
Key experiences Ethiopia shared at the Education World Forum include:
1] Expanding access to education through the construction of schools in rural and underserved communities under the “Education for Generation Initiative.”
2] Developing and implementing policies to strengthen Early Childhood Development (ECD) and pre-primary education(Bu'uura Boruu).
3] Developing and implementing inclusive education policies that support children with disabilities and special learning needs.
4] Promoting mother-tongue instruction in primary schools to improve foundational learning and student participation.
5 ] Advancing gender equity initiatives aimed at increasing girls’ enrollment, participation, and retention in schools.
6 ] Implementing alternative education programs for pastoralist and hard-to-reach communities.
7] Strengthening foundational learning and teacher development to improve the quality, equity, and inclusiveness of education.
Ethiopia reaffirmed its commitment to ensuring equitable, inclusive, and quality education for all by sharing its national reforms and practical experiences in expanding access, improving foundational learning, promoting inclusion, and strengthening teacher development
ኢትዮጵያ በለንደን ከተማ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 ላይ ፍትሃዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ጥራት ያለው የትምህርት ሥርዓት በመገንባት ረገድ ያላትን ልምድ አቅርባለች።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በፎረሙ ላይ ኢትዮጵያ በትምህርት ተደራሽነት፣ አካታችነት እና የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ዙሪያ ያከናወነቻቸውን ተግባራት አብራርተዋል።
በዚህም፦
✅ በገጠርና አገልግሎት በማይደርስባቸው አካባቢዎች ትምህርት ቤቶችን በመገንባት የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋፋት፣
✅ የቅድመ ልጅነት እድገት (ECD) እና የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ለማጠናከር የተወሰዱ እርምጃዎች፣
✅ የአካል ጉዳተኞችንና የልዩ ትምህርት ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች የሚደግፉ አካታች ፖሊሲዎችን መተግበር፣
✅ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርትን በማስፋፋት የተማሪዎችን ተሳትፎና መሰረታዊ ትምህርት ማሻሻል፣
✅ የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎ እና ቆይታ ለማሳደግ የተሰሩ ሥራዎች፣
✅ ለአርብቶ አደርና ለመድረስ አስቸጋሪ ማህበረሰቦች አማራጭ የትምህርት ፕሮግራሞችን መተግበር፣
✅ የትምህርት ጥራትን፣ ፍትሃዊነትንና አካታችነትን ለማጠናከር የመምህራን ልማትን ማበረታታት የሚሉ ቁልፍ ተሞክሮዎች አቅርባዋል።
በመድረኩ ላይ ኢትዮጵያ ለሁሉም ዜጎች ፍትሃዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ጥራት ያለው ትምህርት ለማረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት እንደገና አረጋግጣለች።
በተጨማሪም ክቡር ሚኒስትሩ ጎን ለጎን በተካሄደው የአፍሪካ ትምህርት ሚኒስትሮች መድረክ ላይ “በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻል” ንቅናቄ በህብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ ሰፊ የትምህርት ልማት ተግባራትን በማቅረብ የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካፍለዋል።
May 21, 2026 167
National News

በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሚመሩት የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በለንደኑ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2026 በመሳተፍ ላይ ነው፤

በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራው የኢትዮጵያ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በለንደን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም የትምህርት ፎረም (World Education Forum 2026) ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል።
የዘንድሮው ፎረም "ለጋራ የወደፊት ጊዜ ትምህርት መስጠት፡ ሰላም፣ ፕላኔት፣ ዓላማ እና መንገዶች በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ይህ መድረክ በዓለም አቀፍ ደረጃ በትልቁ የሚጠቀስ የትምህርት እና የክህሎት ሚኒስትሮች ስብሰባ ነው።
በዚህ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም ላይ ከመላው ዓለም የመጡ ሚኒስትሮችን፣ ፖሊሲ አውጪዎችን፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን እና የትምህርት ቴክኖሎጂ መሪዎችን በአጠቃላይ ከ125 አገሮች የመጡ ከ1500 በላይ የሚኒስትሮች የልኡካን ቡድን ተገኝተዋል።
ይህ ታላቅ ፎረም ሚኒስትሮች እና የትምህርት መሪዎች የፖሊሲ ልምዶችን እንዲለዋወጡ፣ አዳዲስ ስልታዊ አጋርነቶችን እንዲፈጥሩ፣ በትምህርት ፋይናንስ እና ማሻሻያዎች ላይ እንዲወያዩ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ትምህርትን ቀጣይ አቅጣጫ ለመቅረጽ ከፍተኛ ዕድል የሚፈጥር መድረክ መሆኑም ተመላክቷል።
ልዑካን ቡድኑ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የትምህርት ሪፎርም እና ተሞክሮዎች ያካፈለ ሲሆን፣ በቀጣይ የሀገሪቱን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል በሚረዱ ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ውይይቶችን አድርጓል።
በዚህ መድረክ ሀገራችን ያላትን ልምድ ያካፈለች ሲሆን በመሠረታዊ ትምህርት፣ በቅድመ ልጅነት እድገት፣ በመምህራን ስልጠና፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በወጣቶች ክህሎት ልማት ላይ ከተለያዩ አገሮች ልምድ ለመቀስም ጠቃሚ አጋጣሚ መሆኑ ተጠቅሷል።
በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራው የኢትዮጵያ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በለንደን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም የትምህርት ፎረም (World Education Forum 2026) ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል።
የዘንድሮው ፎረም "ለጋራ የወደፊት ጊዜ ትምህርት መስጠት፡ ሰላም፣ ፕላኔት፣ ዓላማ እና መንገዶች በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ይህ መድረክ በዓለም አቀፍ ደረጃ በትልቁ የሚጠቀስ የትምህርት እና የክህሎት ሚኒስትሮች ስብሰባ ነው።
በዚህ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎረም ላይ ከመላው ዓለም የመጡ ሚኒስትሮችን፣ ፖሊሲ አውጪዎችን፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን እና የትምህርት ቴክኖሎጂ መሪዎችን በአጠቃላይ ከ125 አገሮች የመጡ ከ1500 በላይ የሚኒስትሮች የልኡካን ቡድን ተገኝተዋል።
ይህ ታላቅ ፎረም ሚኒስትሮች እና የትምህርት መሪዎች የፖሊሲ ልምዶችን እንዲለዋወጡ፣ አዳዲስ ስልታዊ አጋርነቶችን እንዲፈጥሩ፣ በትምህርት ፋይናንስ እና ማሻሻያዎች ላይ እንዲወያዩ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ትምህርትን ቀጣይ አቅጣጫ ለመቅረጽ ከፍተኛ ዕድል የሚፈጥር መድረክ መሆኑም ተመላክቷል።
ልዑካን ቡድኑ በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያን የትምህርት ሪፎርም እና ተሞክሮዎች ያካፈለ ሲሆን፣ በቀጣይ የሀገሪቱን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል በሚረዱ ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ውይይቶችን አድርጓል።
በዚህ መድረክ ሀገራችን ያላትን ልምድ ያካፈለች ሲሆን በመሠረታዊ ትምህርት፣ በቅድመ ልጅነት እድገት፣ በመምህራን ስልጠና፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በወጣቶች ክህሎት ልማት ላይ ከተለያዩ አገሮች ልምድ ለመቀስም ጠቃሚ አጋጣሚ መሆኑ ተጠቅሷል።
May 21, 2026 179
National News

በኢትዮጵያ የትምህርት ቴክኖሎጂን ለማሳደግ ያለመው የ2026 የኤድቴክ (EdTech) ሳምንት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በኢትዮጵያ የትምህርት ቴክኖሎጂ (EdTech) ዘርፍን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመው የ2026 የኤድቴክ ሳምንት በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል።
መርሃ ግብሩን በይፋ የከፈቱት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ማልማትና ጥቅም ላይ ማዋል ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተለይም የትምህርት ስራውን የሚደግፉ ቴክኖሎጂዎች የመማር ማስተማር ስራውን ውጤታማ በማድረግ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ጉልህ ሚና ያላቸው በመሆኑ በስፋት በማልማትና ተደራሽ በማድረግ ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ከዚህ አኳያም የለሙ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ተቋማዊ አሰራር (System) በመቀየር ረገድ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግርን ብሄራዊ አጀንዳ አድርጎ በትኩረት በማስፈጸም የማህበረሠቡን ተጠቃሚነት በመረጋገጥ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን ያመላከቱት ሚኒስቴር ደኤታው በቀጣይም ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የኤድቴክ ፌሎውሺፕ ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች የፈጠራ ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ይህም ለአዳዲስ የፈጠራ ስራ ባለቤት ለሆኑ ወጣቶች ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።
ይህ "የተቀናጀ የትምህርት ቴክኖሎጂ ሁሉን አቀፍ እና የሥርዓተ-ፆታ ምላሽ ሰጪ ለሆነ ትምህርት" በሚል መሪ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ እየተካሄደ ያለው የ2026 የኤድቴክ ሳምንት በትምህርት ሚኒስቴር፣ በሪች ፎር ቼንጅ (Reach for Change) እና በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ትብብር የተዘጋጀ መሆኑም ተመላክቷል።
በኢትዮጵያ የትምህርት ቴክኖሎጂ (EdTech) ዘርፍን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመው የ2026 የኤድቴክ ሳምንት በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በደመቀ ሁኔታ ተከፍቷል።
መርሃ ግብሩን በይፋ የከፈቱት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ማልማትና ጥቅም ላይ ማዋል ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በተለይም የትምህርት ስራውን የሚደግፉ ቴክኖሎጂዎች የመማር ማስተማር ስራውን ውጤታማ በማድረግ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ጉልህ ሚና ያላቸው በመሆኑ በስፋት በማልማትና ተደራሽ በማድረግ ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ከዚህ አኳያም የለሙ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ተቋማዊ አሰራር (System) በመቀየር ረገድ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግርን ብሄራዊ አጀንዳ አድርጎ በትኩረት በማስፈጸም የማህበረሠቡን ተጠቃሚነት በመረጋገጥ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዘርፉ የተገኙ ስኬቶችን ያመላከቱት ሚኒስቴር ደኤታው በቀጣይም ይሄው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የኤድቴክ ፌሎውሺፕ ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች የፈጠራ ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ይህም ለአዳዲስ የፈጠራ ስራ ባለቤት ለሆኑ ወጣቶች ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።
ይህ "የተቀናጀ የትምህርት ቴክኖሎጂ ሁሉን አቀፍ እና የሥርዓተ-ፆታ ምላሽ ሰጪ ለሆነ ትምህርት" በሚል መሪ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ እየተካሄደ ያለው የ2026 የኤድቴክ ሳምንት በትምህርት ሚኒስቴር፣ በሪች ፎር ቼንጅ (Reach for Change) እና በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ትብብር የተዘጋጀ መሆኑም ተመላክቷል።
Mar 26, 2026 1.9K
National News

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥራዎቻቸውን በእውነት፣ በሐቀኝነትና በታማኝነት ሊያከናውኑ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስገነዘቡ።

በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በተዘጋጁ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ፣ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ ደንብ ፣ ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥራዎቻቸውን በእውነት፣ በሐቀኝነትና በታማኝነት ሊያከናውኑ እንደሚገባ አስታውቀዋል።
‎በተቋማቱ የሚካሄዱ የሪፎርም አጀንዳዎች ዓላማ ዩኒቨርስቲዎች ካሉባቸው ተለምዷዊ የአሰራር ልምዶች በማላቀቅ አርአያነት ባለው መልኩ ተልዕኳቸውን እንዲፈጽሙ ማስቻል መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት የአመራር ምልመላ የሚፈለጉ የአመራር ክህሎቶችን መሠረት ያደረገ ግልጽነትና ተዓማኒነት ያለው ሆኖ ከዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ፣ ከኢንዱስትሪና የውጭ ዜጎችና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጭምር በሚጋብዝ መልኩ መዘጋጀቱንም ጠቅሰዋል።
‎ለዩኒቨርስቲዎች የሚመደበው የጥቅል በጀት ስሌት በቀመር ላይ እንዲሁም በግልጽነትና ተጠያቂነት ላይ በተመሠረተ አኳሃን ሊፈጸም እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
‎በየደረጃው ያሉ የዩዩኒቨርስቲ አመራሮች ለሥራቸው የሚያግዛቸውን የአመራር ስልጠና በማግኘት የአመራር ክህሎት እንዲያጎለብቱ የስልጠና ማዕከል መቋቋሙንም አመላክተዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጣቸውን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንዲችሉ እየተሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎የተዘጋጁት ደንብና መመሪያዎችም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ሥራዎቻቸውን በግልጸኝነትና ወጥ የሆነ አሰራር በማስፈን የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችሉ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ደንብና መመሪያዎቹ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ በሙያቸው የሰለጠኑ ብቁና ችሎታ ያላቸው የትምህርት አመራሮችን ወደ ስራ ማስገባት እንደሚያስችሉም ገልጸዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) በበኩላቸው በመድረኩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ፣ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ ደንብ ፣ ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎ውይይት የተደረገባቸው ሰነዶች ተቋማቱ ያሉባቸውን ችግሮች በመፍታት ሀብቶቻቸውን በአግባቡ በማስተዳደር ለታለመለት ዓላማ እንዲያውሉና የትምህርት ጥራት እንዲያስጠብቁ እንደሚያስችሉም አስረድተዋል።
‎በመድረኩ ላይ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በተዘጋጁ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ፣ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ ደንብ ፣ ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥራዎቻቸውን በእውነት፣ በሐቀኝነትና በታማኝነት ሊያከናውኑ እንደሚገባ አስታውቀዋል።
‎በተቋማቱ የሚካሄዱ የሪፎርም አጀንዳዎች ዓላማ ዩኒቨርስቲዎች ካሉባቸው ተለምዷዊ የአሰራር ልምዶች በማላቀቅ አርአያነት ባለው መልኩ ተልዕኳቸውን እንዲፈጽሙ ማስቻል መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት የአመራር ምልመላ የሚፈለጉ የአመራር ክህሎቶችን መሠረት ያደረገ ግልጽነትና ተዓማኒነት ያለው ሆኖ ከዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ፣ ከኢንዱስትሪና የውጭ ዜጎችና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጭምር በሚጋብዝ መልኩ መዘጋጀቱንም ጠቅሰዋል።
‎ለዩኒቨርስቲዎች የሚመደበው የጥቅል በጀት ስሌት በቀመር ላይ እንዲሁም በግልጽነትና ተጠያቂነት ላይ በተመሠረተ አኳሃን ሊፈጸም እንደሚገባም ክቡር ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።
‎በየደረጃው ያሉ የዩዩኒቨርስቲ አመራሮች ለሥራቸው የሚያግዛቸውን የአመራር ስልጠና በማግኘት የአመራር ክህሎት እንዲያጎለብቱ የስልጠና ማዕከል መቋቋሙንም አመላክተዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጣቸውን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንዲችሉ እየተሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
‎የተዘጋጁት ደንብና መመሪያዎችም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ሥራዎቻቸውን በግልጸኝነትና ወጥ የሆነ አሰራር በማስፈን የሚፈለገውን ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችሉ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
‎ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ደንብና መመሪያዎቹ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ በሙያቸው የሰለጠኑ ብቁና ችሎታ ያላቸው የትምህርት አመራሮችን ወደ ስራ ማስገባት እንደሚያስችሉም ገልጸዋል።
‎የከፍተኛ ትምህርት የአስተዳደርና መሠረተ ልማት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) በበኩላቸው በመድረኩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የራስ-ገዝነት የሽግግር መመሪያ፣ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግስት ጥቅል የበጀት ድጋፍ ለመደንገግ የወጣ ደንብ ፣ ለመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አሰያየምን ለመደንገግ የወጣ መመሪያ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎ውይይት የተደረገባቸው ሰነዶች ተቋማቱ ያሉባቸውን ችግሮች በመፍታት ሀብቶቻቸውን በአግባቡ በማስተዳደር ለታለመለት ዓላማ እንዲያውሉና የትምህርት ጥራት እንዲያስጠብቁ እንደሚያስችሉም አስረድተዋል።
‎በመድረኩ ላይ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
Mar 23, 2026 1.8K
National News

ኢትዮጵያ እና ኒውዝላንድ በትምህርቱ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደርጉ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦውንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ አካላት በትምህርት ዘርፉ የነበራቸውን ትብብር አጠናክረው መቀጥል በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።

በዚሁ ውቅት የትምህርት ሚኒስትሩ በትምህርት ሥርዓቱ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለአምባሳደሯ አብርራተውላቸዋል።

እነዚህን የሪፎርም ተግባራት የበለጠ ውጤታማ ለማድረግም ከሀገሪቱ የመልማት ፍላጎት ጋር አብረው በሚሄዱ አዳዲስ የትምህርት መስኮች፣ በከፍተኛ ትምህርት ፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ልማት፣ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ግብዓት አቅርቦትና በመሳሰሉት ላይ የአጋር አካላትን ድጋፍ እንደሚፈልጉ ጠይቀዋል።

 

በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦውን በበኩላቸው ኢትዮጵያ በትምህርቱ ዘርፍ እየተገበረቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራት የሚደነቁ መሆኑን ገልጸው ኒውዝላድ በትምህርቱ ዘርፍ የምታደርገውን ትብብር አጠናክራ መቀጠል እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

በተለይም በነጻ የትምህርት እድል፣ በምሁራን ልውውጥ፣ በመምህራን ስልጠናዎች፣ በትምህርት ቤት ምገባ የእርሻ ልማት፣ የባህል ልውውጥና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ ለሚንስትሩ አብራርተውላቸዋል።

በስተመጨረሻም ሁለቱ ወገኖች በትምህርቱ ዘርፍ በሚኖራቸው ትብብር ዙሪያ ቀጣይ ውይይት ለማድርግና በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ደርሰዋል።

 

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦውንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ አካላት በትምህርት ዘርፉ የነበራቸውን ትብብር አጠናክረው መቀጥል በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።

በዚሁ ውቅት የትምህርት ሚኒስትሩ በትምህርት ሥርዓቱ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ፍትሃዊና ጥራት ያለው ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ለአምባሳደሯ አብርራተውላቸዋል።

እነዚህን የሪፎርም ተግባራት የበለጠ ውጤታማ ለማድረግም ከሀገሪቱ የመልማት ፍላጎት ጋር አብረው በሚሄዱ አዳዲስ የትምህርት መስኮች፣ በከፍተኛ ትምህርት ፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ልማት፣ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ግብዓት አቅርቦትና በመሳሰሉት ላይ የአጋር አካላትን ድጋፍ እንደሚፈልጉ ጠይቀዋል።

 

በኢትዮጵያ የኒውዝላንድ አምባሳደር ኦሊቪያ ኦውን በበኩላቸው ኢትዮጵያ በትምህርቱ ዘርፍ እየተገበረቻቸው ያሉ የሪፎርም ተግባራት የሚደነቁ መሆኑን ገልጸው ኒውዝላድ በትምህርቱ ዘርፍ የምታደርገውን ትብብር አጠናክራ መቀጠል እንደምትፈልግ ገልጸዋል።

በተለይም በነጻ የትምህርት እድል፣ በምሁራን ልውውጥ፣ በመምህራን ስልጠናዎች፣ በትምህርት ቤት ምገባ የእርሻ ልማት፣ የባህል ልውውጥና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንደሚፈልጉ ለሚንስትሩ አብራርተውላቸዋል።

በስተመጨረሻም ሁለቱ ወገኖች በትምህርቱ ዘርፍ በሚኖራቸው ትብብር ዙሪያ ቀጣይ ውይይት ለማድርግና በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ደርሰዋል።

 

Mar 19, 2026 1.7K
National News

ሴቶችን በኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፓለቲካዊ ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደ ሀገር በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞችና አመራሮች "50ኛ ዓመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በድምቀት ከክብረዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ጥራቱን የጠበቀና ፍትሃዊ የትምህርት ተደራሽነትን በማረጋገጥ ሴቶችን በኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ እና ፓለቲካዊ ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደ ሀገር በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
አያይዘውም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና እኩልነት ማረጋገጥ በልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ አይተኬ ሚና ያለው መሆኑን በማንሳት እድሎችን አሟጦ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም መንግስት የሴቶችን ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚ ተሳትፎ ለማሳደግ በወሰዳቸው ቁርጠኛ እርምጃዎች ውጤቶች መታየት መጀመራቸውን ጠቁመው በተለይም ሴቶች በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ እንዲመደቡና የራሳቸውን እንዲሁም የሀገራቸውን ዕጣ ፈንታ እንዲወስኑ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ምህረተክርስቶስ ታምሩ በበኩላቸው ባደረጉት ገለፃ የሴቶች እኩልነት ጉዳይ የአንድ ወቅት ተግባር ሳይሆን ዘላቂ ትኩረት የሚሻ የሰብዓዊ መብትና የልማት ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።
በመጨረሻም በሁሉም የትምህርት እርከኖች የሚገኙ ሴት ተማሪዎችና በስራ ዓለም ያሉ ሴቶች ያላቸውን አቅም ተጠቅመው ለሀገር ብልጽግና የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
የትምህርት ሚኒስቴር ሠራተኞችና አመራሮች "50ኛ ዓመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በድምቀት ከክብረዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት ጥራቱን የጠበቀና ፍትሃዊ የትምህርት ተደራሽነትን በማረጋገጥ ሴቶችን በኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ እና ፓለቲካዊ ዘርፎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደ ሀገር በመከናወን ላይ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና እኩልነት ማረጋገጥ በልማትና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ አይተኬ ሚና ያለው መሆኑን በማንሳት እድሎችን አሟጦ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም መንግስት የሴቶችን ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚ ተሳትፎ ለማሳደግ በወሰዳቸው ቁርጠኛ እርምጃዎች ውጤቶች መታየት መጀመራቸውን ጠቁመው በተለይም ሴቶች በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ እንዲመደቡና የራሳቸውን እንዲሁም የሀገራቸውን ዕጣ ፈንታ እንዲወስኑ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ መሆኑን አብራርተዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ምህረተክርስቶስ ታምሩ በበኩላቸው ባደረጉት ገለፃ የሴቶች እኩልነት ጉዳይ የአንድ ወቅት ተግባር ሳይሆን ዘላቂ ትኩረት የሚሻ የሰብዓዊ መብትና የልማት ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።
በመጨረሻም በሁሉም የትምህርት እርከኖች የሚገኙ ሴት ተማሪዎችና በስራ ዓለም ያሉ ሴቶች ያላቸውን አቅም ተጠቅመው ለሀገር ብልጽግና የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
Mar 18, 2026 1.8K
National News

የተረጋጋ ሀገር እንዲኖር በትምህርት ዘርፉ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትን እያረጋገጡ መሄድ ያስፈልጋል፤ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዳሰነች ወረዳ የተገነባውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት በትምህርት አቅርቦት ረገድ በሁሉም አካባቢ ምንም ልዩነት ሊፈጠር አይገባም ብለዋል።
ይህንንም ለማረጋገጥም በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይም ምቹ የመማሪያ ከባቢን በሁሉም አካባቢ ለመፍጠር “በትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንና የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና መደረጉን አንስተዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ መሆኑን በማመን በከተማና በባለሀብቶች ብቻ ታጥሮ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት በመቀየር በሁሉም አካባቢ ያለ ልዩነት ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በከተማና በገጠር ተገንብተው የአምስተና ስድስት ዓመት ህፃናት እየተማሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
ትምህርት ለሁሉ ነገር ወሳኝ በመሆኑ ልጆቻችንን በአግባቡ በማስተማር የአለምን ፈተና መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ሀገር ተረካቢዎችን ለመፍጠር መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም የትምህርት ሥራ ከፖለቲካ መላቀቅ አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑ ቀርቶ ትምህርት የሁላችን እንዲሆን በማድረግ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዳሰነች ወረዳ የተገነባውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት በትምህርት አቅርቦት ረገድ በሁሉም አካባቢ ምንም ልዩነት ሊፈጠር አይገባም ብለዋል።
ይህንንም ለማረጋገጥም በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይም ምቹ የመማሪያ ከባቢን በሁሉም አካባቢ ለመፍጠር “በትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንና የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና መደረጉን አንስተዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ መሆኑን በማመን በከተማና በባለሀብቶች ብቻ ታጥሮ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት በመቀየር በሁሉም አካባቢ ያለ ልዩነት ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በከተማና በገጠር ተገንብተው የአምስተና ስድስት ዓመት ህፃናት እየተማሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
ትምህርት ለሁሉ ነገር ወሳኝ በመሆኑ ልጆቻችንን በአግባቡ በማስተማር የአለምን ፈተና መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ሀገር ተረካቢዎችን ለመፍጠር መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም የትምህርት ሥራ ከፖለቲካ መላቀቅ አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑ ቀርቶ ትምህርት የሁላችን እንዲሆን በማድረግ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
Mar 01, 2026 2.9K
National News

በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።

በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሞራቴ ከተማ የተገነባው የአሞራቴ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል፤ ተጨማሪ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት እቅድ ተይዟል።
በትምህርት ሚኒስቴርና በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች አኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ዛሬ በዳሰነች የተመረቀው አዳሪ ትምህርት ቤት አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የራሱን ሥራ ሲሰራ ልጆቹ ተረጋግተው የሚማሩበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
እነሱን ሳናስተምር ይች ሀገር ለሁላችንም እኩል ነች ማለት ከባድ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ትልቅ ደስታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በቀጣይ ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን በመለየት 1452 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ ሲሆን በዳሰነችም ሁለት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይገነባል ብለዋል።
መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ከአምስት ዓመት ጀምሮ ለማስተማር በሰጠው ልዩ ትኩረት ባለፉት ዓመታት ከ34ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
ይች ሀገር የተወሰኑ ሰዎች ሀገር ሳትሆን የሁሉም የኢትዮጵያውያን በመሆኗ የተረጋጋ ሀገር እንዲኖረን በትምህርት ዘርፉ ያለልዩነት እኩል ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው መንግስት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስተካከል ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት በተሰራው ስራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት ለዚህ አካባቢ ትርጉሙ ትልቅ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሻለ ነገ እንዲኖር ዛሬ የተሻለ ነገር እየሰራ ላለው ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል ።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራዲስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች ከዚህ ቀደም በገነባቸው ትምህርት ቤቶች በርካታ ሙሁራን መውጣታቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤትም ነገ ሀገር መምራት የሚችሉ ልጆች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልፀው ትምህርት ቤቱ ዘላቂነት እንዲኖረው በባለቤትነት መንከባከብ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሞራቴ ከተማ የተገነባው የአሞራቴ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል፤ ተጨማሪ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት እቅድ ተይዟል።
በትምህርት ሚኒስቴርና በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች አኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ዛሬ በዳሰነች የተመረቀው አዳሪ ትምህርት ቤት አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የራሱን ሥራ ሲሰራ ልጆቹ ተረጋግተው የሚማሩበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
እነሱን ሳናስተምር ይች ሀገር ለሁላችንም እኩል ነች ማለት ከባድ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ትልቅ ደስታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በቀጣይ ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን በመለየት 1452 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ ሲሆን በዳሰነችም ሁለት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይገነባል ብለዋል።
መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ከአምስት ዓመት ጀምሮ ለማስተማር በሰጠው ልዩ ትኩረት ባለፉት ዓመታት ከ34ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
ይች ሀገር የተወሰኑ ሰዎች ሀገር ሳትሆን የሁሉም የኢትዮጵያውያን በመሆኗ የተረጋጋ ሀገር እንዲኖረን በትምህርት ዘርፉ ያለልዩነት እኩል ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው መንግስት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስተካከል ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት በተሰራው ስራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት ለዚህ አካባቢ ትርጉሙ ትልቅ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሻለ ነገ እንዲኖር ዛሬ የተሻለ ነገር እየሰራ ላለው ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል ።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራዲስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች ከዚህ ቀደም በገነባቸው ትምህርት ቤቶች በርካታ ሙሁራን መውጣታቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤትም ነገ ሀገር መምራት የሚችሉ ልጆች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልፀው ትምህርት ቤቱ ዘላቂነት እንዲኖረው በባለቤትነት መንከባከብ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
Feb 28, 2026 2.3K
National News

የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ትምህርት ሚኒስቴር ከሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባው የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው እለት ተመርቋል።
ትምህርት ቤቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተገኝተው መርቀውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ዛሬ የተመረቀው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደ ሀገር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
ከለውጡ ወዲህ እንደ በፊቱ የመሠረት ድጋይ አስቀምጦ መሄድ ቀርቷል ያሉ ሲሆን በትምህርት ሴክተሩ ፕሮጀክት ጀምሮ በአጠረ ጊዜ መጨረስ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሴክተሩ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ ወድቆ በመቆየቱ ከዚህ ለማላቀቅ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት እየተተገበሩ መሆኑንና በተለይም ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ መስራትና መተማመን የሚችል ትውልድ ለመፍጠር እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ በመሆኑ በሁሉም የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲኖሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም ባለፉት አመታት ከ34ሺ በላይ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ 1452 ትምህርት ቤቶች በ726 ወረዳዎች በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሎች ትብብር እንደሚገነቡ ጠቁመዋል ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገትና ለዜጎች ከፍ ማለት ወሳኝ መሣሪያ በመሆኑ መንግስት በሪፎርሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
የትምህርት ሴክተሩ እጅግ ስኬታማ ከሆኑ ተቋማት ውስጥ የሚጠቀስ መሆኑን አንስተው በተለይ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተገኘው ውጤት የሚደነቅ ነውም ብለዋል።
ይህ ትምህርት ቤትም ስታንዳርዱን ጠብቆ የተገነባ በመሆኑ ህብረተሰቡ በባለቤትነት ጠብቆ በመከባከብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ሰባስቲያን ብራንስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች በትምህርት፣በጤና፣ በምግብ ዋስተናና በውሃ አቅርቦት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ሰፊ እድል ይዞ የመጣ በመሆኑ ውጤታማ ለመሆን ተማሪዎች ጠንክረው እንዲማሩም አሳስበዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ትምህርት ሚኒስቴር ከሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባው የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው እለት ተመርቋል።
ትምህርት ቤቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተገኝተው መርቀውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ዛሬ የተመረቀው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደ ሀገር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
ከለውጡ ወዲህ እንደ በፊቱ የመሠረት ድጋይ አስቀምጦ መሄድ ቀርቷል ያሉ ሲሆን በትምህርት ሴክተሩ ፕሮጀክት ጀምሮ በአጠረ ጊዜ መጨረስ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሴክተሩ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ ወድቆ በመቆየቱ ከዚህ ለማላቀቅ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት እየተተገበሩ መሆኑንና በተለይም ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ መስራትና መተማመን የሚችል ትውልድ ለመፍጠር እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ በመሆኑ በሁሉም የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲኖሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም ባለፉት አመታት ከ34ሺ በላይ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ 1452 ትምህርት ቤቶች በ726 ወረዳዎች በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሎች ትብብር እንደሚገነቡ ጠቁመዋል ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገትና ለዜጎች ከፍ ማለት ወሳኝ መሣሪያ በመሆኑ መንግስት በሪፎርሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
የትምህርት ሴክተሩ እጅግ ስኬታማ ከሆኑ ተቋማት ውስጥ የሚጠቀስ መሆኑን አንስተው በተለይ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተገኘው ውጤት የሚደነቅ ነውም ብለዋል።
ይህ ትምህርት ቤትም ስታንዳርዱን ጠብቆ የተገነባ በመሆኑ ህብረተሰቡ በባለቤትነት ጠብቆ በመከባከብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ሰባስቲያን ብራንስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች በትምህርት፣በጤና፣ በምግብ ዋስተናና በውሃ አቅርቦት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ሰፊ እድል ይዞ የመጣ በመሆኑ ውጤታማ ለመሆን ተማሪዎች ጠንክረው እንዲማሩም አሳስበዋል።
Feb 27, 2026 1.1K
National News

ኢትዮጵያ የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተጠቆመ።

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች 130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን '' አድዋ 130፣ ከአኩሪ ታሪክ፣ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል አገራዊ መሪ ቃል አክብረዋል።
‎የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አድዋ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች ነጻነት ህያው ተምሳሌት በመሆኑ አባቶቻችንና እናቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነትና ላጎናጸፉን ድል ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።
‎ትምህርት ለምናደርገው የእድገትና የብልጽግና ጉዞ ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ ጅምር ስራዎቻችንን አልቆ በመፈጸም እንደሚገባ ክብርት ሚኒስትር ደኤታ አስገንዝበዋል።
‎አገራችን ለዜጎቿ የተመቸችና የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ የትምህርት ዘርፉ ተዋናዮች የበኩላቸውን ድርሻ በላቀ የአገር ፍቅርና ስሜት መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ክብርት ወ/ሮ አየለች አንስተዋል።
‎የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከመሠረቱ በህጻናት ላይ መስራት የሚገባን መሆኑን በመረዳት ለህጻት ትምህርት የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
‎ዳር ድንበሮቻችንን ለመጠበቅና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ለማዝለቅ አንድነታችንን ማጠናከር እንደሚገባም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል።
‎የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ለአንድነታችንና ለብሔራዊ ጥቅማችን ባለው ፋይዳ ላይ ግንዛቤ መፍጠር የክብረ በዓሉ ዓላማ መሆኑን አስተው አድዋ በዓለም ታሪክ አፍሪካዊት አገር ቅኝ ግዛትን በጦር ኃይል ያሸነፈችበትና በደማቅ ቀለም የተጻፈ ታሪካዊ ተምሳሌት የሆነችበት አኩሪ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ አቶ ዑመር ይማም በበኩላቸው የአድዋ ድል ብሔራዊ የአንድነትና የአሸናፊነት ምልክት መሆኑን አስረድተዋል።
‎የብሄራዊ ጥቅም የመጀመሪያው መነሻ ሉዓላዊነት በመሆኑ በሉዓላዊነት ጉዳይ ላይ ዜጎች በአንድነት ሊቆሙ እንደሚገባም ገልጸዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ በተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች 130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን '' አድዋ 130፣ ከአኩሪ ታሪክ፣ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል አገራዊ መሪ ቃል አክብረዋል።
‎የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አድዋ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች ነጻነት ህያው ተምሳሌት በመሆኑ አባቶቻችንና እናቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነትና ላጎናጸፉን ድል ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።
‎ትምህርት ለምናደርገው የእድገትና የብልጽግና ጉዞ ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ ጅምር ስራዎቻችንን አልቆ በመፈጸም እንደሚገባ ክብርት ሚኒስትር ደኤታ አስገንዝበዋል።
‎አገራችን ለዜጎቿ የተመቸችና የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ የትምህርት ዘርፉ ተዋናዮች የበኩላቸውን ድርሻ በላቀ የአገር ፍቅርና ስሜት መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ክብርት ወ/ሮ አየለች አንስተዋል።
‎የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከመሠረቱ በህጻናት ላይ መስራት የሚገባን መሆኑን በመረዳት ለህጻት ትምህርት የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
‎ዳር ድንበሮቻችንን ለመጠበቅና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ለማዝለቅ አንድነታችንን ማጠናከር እንደሚገባም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል።
‎የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ለአንድነታችንና ለብሔራዊ ጥቅማችን ባለው ፋይዳ ላይ ግንዛቤ መፍጠር የክብረ በዓሉ ዓላማ መሆኑን አስተው አድዋ በዓለም ታሪክ አፍሪካዊት አገር ቅኝ ግዛትን በጦር ኃይል ያሸነፈችበትና በደማቅ ቀለም የተጻፈ ታሪካዊ ተምሳሌት የሆነችበት አኩሪ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ አቶ ዑመር ይማም በበኩላቸው የአድዋ ድል ብሔራዊ የአንድነትና የአሸናፊነት ምልክት መሆኑን አስረድተዋል።
‎የብሄራዊ ጥቅም የመጀመሪያው መነሻ ሉዓላዊነት በመሆኑ በሉዓላዊነት ጉዳይ ላይ ዜጎች በአንድነት ሊቆሙ እንደሚገባም ገልጸዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ በተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Feb 27, 2026 1.1K
National News

እንደ ሀገር የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ባልሆነባቸው ወረዳዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ የትምህርት ቤት ግንባታ ለማካሄድ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ይገኛል።

ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለሟሟላትና ለማሻሻል በቀረጸው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል።
በተለይም ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ትኩረት በመስጠት እና በትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ነጻና የግዴታ ትምህርት እንዲሆን በማመላከት ከ34000 በላይ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል።
ባለፉት ዓመታት እነዚህ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም የነበረውን ክፍተት በሚፈለገው ልክ መሙላት ባለመቻሉ በርካታ ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል፤ ይንንም ለመቅረፍና ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በዚህም ‎ትምህርት ቤቶቹን ለመገንባት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ያልሆነባቸው አካባቢዎችና የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ወረዳዎች ልየታ መደረጉም ተገልጿል።
በነዚህ በተለዩ ወረዳዎች ለትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር በውጤት ተኮር የገንዘብ ድጋፍ ስርዓት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ ግንባታውን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
ከሚገነቡት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው የዋጋ ጥናት 726ቱ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ ይሆናል። እነዚህ የትምህርት ተቋማት የሚገነቡት ክልሉ በተጠቀሱት ወረዳዎች ወይም አካባቢዎች ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰራው ልክ በክልሉ በጀት ወይንም ከማህበረሰቡ አሰባስቦ መገንባት የሚችል ከሆነ ብቻ ነው።
በዚህም በቀጣይ 6 ወራት ትምህርት ሚኒስቴር 726 እንዲሁም ክልሎች በተመሳሳይ 726 በአጠቃላይ 1452 የሚደርሱ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመላ ሀገሪቱ ለመገንባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ዲዛይን የተሰራ ሲሆን እንደየ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ መጠነኛ ለውጥ እንዲኖራቸው እንደሚደረግና ቢያንስ ሁለት የመማሪያ ፣ የመመገቢያ ፣ የህጻናት ማረፊያ ፣ የመምህራን ቢሮ፣ የመጸዳጃ ክፍሎችና ህጻናትን ለፈጠራ በማነሳሳት ሁለንተናዊ እድገታቸው ላይ አወንታዊ ሚና የሚጫወቱባቸው የመጫወቻ ቦታዎች እንደሚኖራቸው ተደርጎ መዘጋጀቱም ተጠቁሟል።
‎የእነዚህ ትምህርት ቤቶቹ መገንባት ሁሉም የኢትዮጵያ ህጻናት አንደኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት ቢያንስ ሁለት ዓመት የቅድመ አንደኛ ደረጃ የዝግጁነት ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችላቸውም ይሆናል።
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለሟሟላትና ለማሻሻል በቀረጸው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል።
በተለይም ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ትኩረት በመስጠት እና በትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ነጻና የግዴታ ትምህርት እንዲሆን በማመላከት ከ34000 በላይ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል።
ባለፉት ዓመታት እነዚህ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም የነበረውን ክፍተት በሚፈለገው ልክ መሙላት ባለመቻሉ በርካታ ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል፤ ይንንም ለመቅረፍና ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በዚህም ‎ትምህርት ቤቶቹን ለመገንባት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ያልሆነባቸው አካባቢዎችና የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ወረዳዎች ልየታ መደረጉም ተገልጿል።
በነዚህ በተለዩ ወረዳዎች ለትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር በውጤት ተኮር የገንዘብ ድጋፍ ስርዓት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ ግንባታውን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
ከሚገነቡት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው የዋጋ ጥናት 726ቱ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ ይሆናል። እነዚህ የትምህርት ተቋማት የሚገነቡት ክልሉ በተጠቀሱት ወረዳዎች ወይም አካባቢዎች ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰራው ልክ በክልሉ በጀት ወይንም ከማህበረሰቡ አሰባስቦ መገንባት የሚችል ከሆነ ብቻ ነው።
በዚህም በቀጣይ 6 ወራት ትምህርት ሚኒስቴር 726 እንዲሁም ክልሎች በተመሳሳይ 726 በአጠቃላይ 1452 የሚደርሱ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመላ ሀገሪቱ ለመገንባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ዲዛይን የተሰራ ሲሆን እንደየ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ መጠነኛ ለውጥ እንዲኖራቸው እንደሚደረግና ቢያንስ ሁለት የመማሪያ ፣ የመመገቢያ ፣ የህጻናት ማረፊያ ፣ የመምህራን ቢሮ፣ የመጸዳጃ ክፍሎችና ህጻናትን ለፈጠራ በማነሳሳት ሁለንተናዊ እድገታቸው ላይ አወንታዊ ሚና የሚጫወቱባቸው የመጫወቻ ቦታዎች እንደሚኖራቸው ተደርጎ መዘጋጀቱም ተጠቁሟል።
‎የእነዚህ ትምህርት ቤቶቹ መገንባት ሁሉም የኢትዮጵያ ህጻናት አንደኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት ቢያንስ ሁለት ዓመት የቅድመ አንደኛ ደረጃ የዝግጁነት ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችላቸውም ይሆናል።
Feb 23, 2026 1.1K
National News

በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ለአይነ ስውራን የተዘጋጁ የ2ኛ ደረጃ የብሬል መጽሐፍት እየተጓጓዙ ነው።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመጀመሪያው ዙር ለስርጭት የተዘጋጁ የብሬል መጽሀፍቱን የስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።
‎ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመጽሐፍቱን ስርጭት ሂደት ምልከታ ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ጥራት፣አግባብነት ፣ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋጥ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛል ብለዋል።
‎ከሪፎርም ስራዎች መካከልም የተሻሻለውን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ መነሻ በማድረግ አዲስ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ ተግባራዊ መደረጉን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ገልጸዋል።
‎ተግባራዊ በተደረገው ሥርዓተ ትምህርት መሠረትም ተማሪዎችና መምህራን የሚገለገሉባቸውን የመማሪያና የማስተማሪያ መጽሀፍት አንድ ለአንድ ለማድረስ ሲሰራ መቆየቱንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል።
‎ሁሉም ዜጎች የመማርና የመማሪያ ግብዓቶችን ማግኘት መብት እንዳላቸው ያስገነዘቡት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ዜጎች በሁሉም ረገድ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
‎ለስርጭት የተዘጋጁት የብሬል መጽሐፍት አይስውራን ተማሪዎች በቂ የመማሪያ መጽሐፍት አግኝተው ራሳቸውን በማብቃት ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል እድል እንዲያገኙና በእውቀትና በክህሎት ብቁ ሆነው እንዲገኙ እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።
‎የቅድመ አንደኛና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ ከ 23.9 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው እየተሰራጩና እየተጓጓዙ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
‎የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ በበኩላቸው በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሂደት ለስርጭት የተዘጋጁት የ2ኛ ደረጃ የብሬል መማሪያ ማስተማሪያ መጽሐፍት በስድስት (6) የትምህርት ዓይነቶች የተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
‎የብሬል መጽሀፍቱ ለሁሉም ክልል አይነ ስውራን ተማሪዎች መታተማቸውን የገለጹት ወ/ሮ ዛፉ በአሁኑ ወቅት ታትመው የተጠናቀቁት የብሬል መጽሐፍት ከማዕከል ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከሰኞ ጀምሮ እንደሚጓጓዙ ጠቁመዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመጀመሪያው ዙር ለስርጭት የተዘጋጁ የብሬል መጽሀፍቱን የስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።
‎ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመጽሐፍቱን ስርጭት ሂደት ምልከታ ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ጥራት፣አግባብነት ፣ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋጥ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛል ብለዋል።
‎ከሪፎርም ስራዎች መካከልም የተሻሻለውን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ መነሻ በማድረግ አዲስ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ ተግባራዊ መደረጉን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ገልጸዋል።
‎ተግባራዊ በተደረገው ሥርዓተ ትምህርት መሠረትም ተማሪዎችና መምህራን የሚገለገሉባቸውን የመማሪያና የማስተማሪያ መጽሀፍት አንድ ለአንድ ለማድረስ ሲሰራ መቆየቱንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል።
‎ሁሉም ዜጎች የመማርና የመማሪያ ግብዓቶችን ማግኘት መብት እንዳላቸው ያስገነዘቡት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ዜጎች በሁሉም ረገድ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
‎ለስርጭት የተዘጋጁት የብሬል መጽሐፍት አይስውራን ተማሪዎች በቂ የመማሪያ መጽሐፍት አግኝተው ራሳቸውን በማብቃት ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል እድል እንዲያገኙና በእውቀትና በክህሎት ብቁ ሆነው እንዲገኙ እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።
‎የቅድመ አንደኛና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ ከ 23.9 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው እየተሰራጩና እየተጓጓዙ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
‎የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ በበኩላቸው በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሂደት ለስርጭት የተዘጋጁት የ2ኛ ደረጃ የብሬል መማሪያ ማስተማሪያ መጽሐፍት በስድስት (6) የትምህርት ዓይነቶች የተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
‎የብሬል መጽሀፍቱ ለሁሉም ክልል አይነ ስውራን ተማሪዎች መታተማቸውን የገለጹት ወ/ሮ ዛፉ በአሁኑ ወቅት ታትመው የተጠናቀቁት የብሬል መጽሐፍት ከማዕከል ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከሰኞ ጀምሮ እንደሚጓጓዙ ጠቁመዋል።
Feb 16, 2026 1.1K
Recent News
Follow Us