News Detail
ትምህርት ሚኒስቴር እና ብሪትሽ ካዉንስል በከፍተኛ ትምህርት የሰላም ጉዳይ ላይ በጋራ ለመስራት የሚያሥችላቸዉን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡
በስነስርዓቱ ላይ የፕሮጀክቱ የምስራቅ አፍሪካ ቀጠና አስተባባሪ ዶ/ር ሃላ ኑር፣ የብሪትሽ ካዉንስል ምክትል ዳይሬክተር ሰላማዊት አለማየሁን ጨምሮ ከብሪትሽ ካዉንስል፣ የትምህርት ሚኒስቴር ሀላፊዎች እንዲሁም ፕሮጀክቱ የሚተገበርባቸዉ የሀዋሳ፣ጅማ እና ባህርዳር ዩኒቨርስቲዎች ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡
ፕሮጀክቱ በሁለቱ አገራት መካከል ያለዉን የረጅም ጊዜ አጋርነት ማጠናከር፣ ዩኒቨርስቲዎች ግጭትን በመከላከል እና የሰላም ግንባታ ያላቸዉን ሚና ማጎልበት እና ስርዓተ ጾታንና ከባቢያዊ ሁኔታን መሰረት ያደረጉ ሰላምን የሚመለከቱ ምርምሮች መደገፍ ላይ ያተኮረ ነው።
በሂደት አገራዊ፣ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ደረጃ በሰላም ጉዳይ በጋራ መስራትን መነሻ ያደረገ ትብብርን የማጠናከር ዓላማ አለዉ፡፡
ስምምነቱ የዩኒቨርስቲ ለሰላም ትምህርትን በአካባቢያዊ ግጭት ወቅት መተግበር የተባለዉ ፕሮጀክት በአዉሮፓ ህብረት እናያለን ብሪትሽ ካዉንስል የገንዘብ ድጋፍ በብሪትሽ ካዉንስል በምስራቅ አፍሪካ ኢትዮጵያንና ሱዳንን ማዕከል አድርጎ ይተገበራል ተብሏል፡፡
Recent News
የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ።
Feb 27, 2026
አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርስቲ አመራሮች ኃላፊነታቸውን በትክክል እንዲወጡ ተጠየቀ ።
Feb 13, 2026