News Detail
ዩኒቨርሲቲዎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ (STEM) ማዕከላት የሚሰሩ ስራዎችን ተቋማዊ በማድረግ በባለቤትነት ሊመሩ እንደሚገባ ተገለጸ
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ (STEM) ማዕከላትን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ዩኒቨርሲቲዎች በማዕከላት የሚሰሩ ስራዎችን ተቋማዊ በማድረግ በባለቤትነት ሊመሩ እንደሚገባ ገልፀዋል።
በማዕከላት የሚሰሩ ስራዎችን ተቋማዊ ለማድረግ በመዋቅር እና አሰራር ማስደገፍ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባም ሚኒስቴር ዴኤታው ተናግረዋል።
በመድረኩ የSTEM ማእከላት በዩኒቨርስቲዎች ማቋቋም ተግባራዊ ትምህርት ለማጠናከር እና አካባቢያዊ ችግሮችን የሚፈታ ትውልድ ለመፍጠር ቁልፍ ሚና እንዳለውም ተጠቁሟል።
በቀጣይ አዳዲስ የሚከፈቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምህንድስና ሂሳብ ማእከላትን በሰው ሃይልና በቁሳቁስ ማጠናከር፣ የተማሪዎችና መምህራን መረጃ መያዝ፣ መንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር ማእከላትን በማጠናከር ዙሪያ የጋራ እቅድ ማውጣት እና መተግበር እንደሚገባም በውይይቱ ተነስቷል።
የዩኒቨርሲቲዎች የSTEM ማእከላት አስተባባሪዎች በበኩላቸው በየማእከላቱ እያጋጠሙ ስላሉ የግብአት፣ የመዋቅር ፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል እና ቴክኖሎጂ ችግሮች አንስተው ውይይት አካሄደዋል።
እስካሁን በ33 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የSTEM ማእከላት ተቋቁመዋል።
Recent News
የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ።
Feb 27, 2026
አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርስቲ አመራሮች ኃላፊነታቸውን በትክክል እንዲወጡ ተጠየቀ ።
Feb 13, 2026