News Detail
Apr 04, 2024
814 views
የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደርን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የጃፓን ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደርን Shibata Hironori በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ውይይት ያደረጉ ሲሆን በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት የትምህርት ዘርፍ ትብብር ዙሪያ በጋራ ለመስራት ስምምነት አድርገዋል።
ክቡር አምባሳደር Shibata Hironori ሀገራቸው አንጋፋውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለማገዝና ከጃፓን ዩኒቨርስቲዎች ጋር ለማስተሳሰር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ክቡር አምባሳደሩ አክለውም ዩኒቨርስቲው ኦቶኖመስ ለመሆን የሚያደርገውን ሂደት ለመደገፍና ከዩኒቨርስቲው ጋር በምርምር ስራዎች ዙሪያ በጋራ ለመስራት፣ ፕሮፌሰሮች የሚያደርጉትን የልምድ ልውውጥ ለመደገፍ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
በተጨማሪም በሁለቱ ወገኖች ውይይት የጃፓን አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (JICA) አራት (4) የሚሆኑ የአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶችን በአዲሲቷ ኢትዮጵያ የት/ቤቶች ዲዛይን መሰረት ገንብቶ ለማስረከብ ስምምነት ተደርጓል።
እንደ ክቡር አምባሳደሩ ገለጻ ሀገራቸው የሁለቱን እህትማማች ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር ሀያ (20) የሚሆኑ በሂሳብና በሳይንስ ትምህርቶች ላይ የሚሰሩ ጃፓናውያን በጎ ፈቃደኞች እንደምትልክ ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም ለስምምነቱ ተግባራዊነት ሁለቱም ወገኖች በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸው ውይይታቸውን አጠናቀዋል።
Recent News
የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና
Jul 23, 2024
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር ውይይት አደረጉ
Jul 18, 2024
ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈታናን አስጀመሩ
Jul 10, 2024
አንጋፋው፣ ስመጥሩና ራስ ገዝ የሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስመረቀ
Jul 08, 2024
በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዙሪያ ከጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ
Jun 25, 2024
2ኛው አመታዊ አገር አቀፍ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ጉባኤ ተካሄደ
Jun 27, 2024