News Detail
Apr 11, 2024
903 views
የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደርን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
የትምህርት ሚንስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደርን Jorge Fernando Lefebre Nicolas በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን ውይይታቸውም በኢትዮጵያና በኩባ የህክምና ትምህርት ተቋማት መካከል የተቋም ተቋም ግንኙነትን ማጠናከር፣ የምርምር ስራዎችን በጋራ መስራት፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮችና የህክምና ባለሙያዎች ልወውጥ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነበር።
ክቡር ሚኒስትሩ ከክቡር አምባሳደሩ ጋር በነበራቸው ውይይትም የአንጋፋው የያሬድ የሙዚቃ ት/ቤትን ለማጠናከር ከአፍሮ ኪዩባን ባህላዊ ማዕከል ጋር በጋራ በሚሰሩበት ዙሪያ ስምምነት አድርገዋል። የተቋማቱ ስምምነት የሀገራቱን የባህላዊ ሙዚቃ ልውውጥ የሚያሳድግ ሲሆን ለያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ደግሞ አለምአቀፍ የሙዚቃ ባህል ልውውጥ ለማድረግ እንዲችል እድል የሚሰጥ እንደሆነ ተገልጿል።
Recent News
የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና
Jul 23, 2024
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር ውይይት አደረጉ
Jul 18, 2024
ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈታናን አስጀመሩ
Jul 10, 2024
አንጋፋው፣ ስመጥሩና ራስ ገዝ የሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስመረቀ
Jul 08, 2024
በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዙሪያ ከጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ
Jun 25, 2024
2ኛው አመታዊ አገር አቀፍ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ጉባኤ ተካሄደ
Jun 27, 2024