News Detail
Oct 30, 2020
680 views
የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት በቴክኖሎጂ የተደገፋ እንደሚሆን ተገለፀ።
የትምህርት ሚኒስቴር ከሁሉም ክልሎች ከተወጣጡ የመምህራንና ትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ፈቃድ ባለሙያዎች ጋር እየተወያየ ነው።
በውይይቱም የ 2012 ዓ.ም እቅድ አፈፃፀም እና የ 2013ዓ.ም እቅድ ይቀርባል።።
በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ዳይሬክተር ወ/ሮ ካሳነሽ አለሙ የትምህርት ዘርፉን ጥራት የሚለካበት አንዱ መንገድ የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና እድሳት በመሆኑ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራበት መሆኑን ገልፀዋል።
በውይይት መድረኩ የተመዛኞችን የምዘና ውጤትና ትንተናን ጨምሮ ከምዝገባ እስከ ሰርቲፊክሽን ድረስ ያለውን ሂደት የሚያሳይ በቴክኖሎጅ የተደገፈ ዳታ ቤዝ ትውውቅ ይደረጋል፡፡
በመድረኩም የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳድሮች የመምህራንና ትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ፈቃድ የ2012 በጀት ዓመት ሪፖርት ይቀርባል።
በቀጣይም የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ምዘና የጥናት ሰነድ ላይና ከመምህራን ትምህርት ኮሌጅ ተመርቀው በሚወጡ መምህራን የሙያ ብቃትና ሌሎች የትኩረት አቅጣጫዎች ዘሪያ ውይይት የሚደረግ ይሆናል።