News Detail

የሀገር ውስጥ ዜና
Jul 17, 2020 1.4K views

ከ8ኛና 12ኛ ክፍል ውጭ ያሉ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ ክፍል ተዛውረው እንዲማሩ ተወሰነ፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ከ8ኛና 12ኛ ክፍል ውጭ ያሉ ተማሪዎች  ወደ ቀጣዩ ክፍል ካለፈተና ተዛውረው በዚህ አመት ያመለጣቸውን ትምህርት እስከ 1 ወር ከ15 ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ አካክሰው እንዲማሩ ተወስኗል፡፡

የቀጣይ አመት የትምህርት ምዝገባ ጊዜ ነሃሴ መጨረሻ ሳምንት ጀምሮ እንደሚጀመር የተገለፀ ሲሆን ከዚህ የጊዜ ሰሌዳ በፊት የመንግስትም ሆነ የግል ትምህርት ቤቶች ምንም አይነት ምዝገባ ማካሄድ እንደማይችሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ተናግረዋል፡፡

Recent News
Follow Us