News Detail

የሀገር ውስጥ ዜና
Aug 27, 2020 533 views

የ ትምህርት ሚኒስቴር በፊንላንድ መንግስት ይሰጥ የነበረውን ድጋፍ እና ትብብር ሲመሩ ለነበሩት ባለሙያ ሽኝት አካሄደ፡፡

የ ትምህርት ሚኒስቴር በፊንላንድ መንግስት ይሰጥ የነበረውን ቴክኒካል እና የ ገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም የ አጋር ድርጅቶች የ ጋራ ትብብርን ሲመሩ ለቆዩት ዶ/ር ሳይ ቫይረን በ ጽህፈት ቤቱ ሽኝት አካሂዷል፡፡

ዶ/ር ሳይ  ላለፉት ሶስት አመታት  በ ፊንላንድ መንግስት ድጋፍ እየተከናወነ ያለውን  የ አጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ለ ፍትሃዊነት  ፕሮጀክት እና የአጋር ድርጅቶች የጋራ ትብብርን ሲመሩ ቆይተዋል፡፡

በሽኝት ስነስርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስቴሩ ዶ/ር ኢንጂ. ጌታሁን መኩሪያ  ዶ/ር ሳይ በ ትምህርት ዘርፉ ላበረከቱት አስተዋፆ እና  ለሰጡት የ ሶስት አመት አገልግሎት  ምስጋና  አቅርበዋል፡፡

በ ትምህረት ዘርፍ  በተለይም ልዩ ፍላጎት  እና አካቶ ትምህርት ላይ  የ ፊንላንድ  መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን  ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

በቀጣይም  የፊንላንድ  መንግስት ለ ትምህርት ዘርፉ  የሚያደርገውን  የገንዘብ ድጋፍ ለማጠናከር በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተካሂዷል፡፡

Recent News
Follow Us