News Detail
Aug 27, 2020
545 views
የትምህርት ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂ ጌታሁን መኩሪያ በኢትዮጵያ የጀርመን መንግስት አምባሳደርን ተቀብለው አነጋገሩ ፡፡
የ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂ ጌታሁን መኩሪያ በ ኢትዮጵያ አዲስ የተሸሙትን የጀርመን አምባሳደር ስቴፈን አውርንን በ ቢሯቸው ተቀብለው በተለያዩ ትምህርት ነክ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡
በ ኢትዮጵያ የጀርመን መንግስት አምባሳደር ሆነው የመጡት ስቴፈን አውርን በ ትምህርት እና ስልጠና ዘርፍ የ ጀርመን መንግስት ሲያደርገው የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
በ አጠቃላይ የ ትምህርት ዘርፍ በተለይም በ ትምህርት ፍኖተ ካርታው ላይ የተቀመጠውን የ ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ላይ ሰርዕተ ትምህርት ዝግጅት እና ትግበራ ለማጠናከር በ ሚያስችል ቀጣይ ስራዎች ላይ ድጋፍ ለማድረግ በሚያስችል ሁኔታ ላይ የ ሁለትዪሽ ውይይትም አካሂደዋል፡፡
የ ጀርመኑ አምባሳደር በቀጣይ የስራ ዘመናቸው ከ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር የተሻሉ ስራዋችን ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ያረጋገጡ ሲሆን፡፡
የ ትምህርት ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂ ጌታሁን መኩሪያ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከ ጀርመን ብዙ ልምዶችን እና ድጋፎችን እንደምትፈልግ በመግለፅ ለ አምባሳደሩ መልካም የስራ ዘመን ተመኝተዋል፡፡