News Detail
May 23, 2024
739 views
ሶስት ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ፍጻሜ ውድድር ለመሳተፍ ቻይና ገቡ።
የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ለዓለም አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የተዘጋጀ አመታዊ ውድድር ነው።
ሁዋዌ በየዓመቱ የሚያካሂደው ይህ ውድድር ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን ጨምሮ ከመላው አለም የተውጣጡ ተማሪዎችን ያሳትፋል። ድርጅቱ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር አገር አቀፍ ውድድር ሲያካሂድ ቆይቷል።
በውድድሩም የኢትዮጵያ ቡድን በሶስት ቡድኖች የተደራጁ ዘጠኝ ተማሪዎችን ይዞ ከዘጠኙ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ማሊ፣ ካሜሩን፣ ሴኔጋል፣ አልጄሪያ፣ ቱኒዚያ፣ ሊቢያ፣ ግብፅ እና ሞሮኮ) ከተውጣጡ ተማሪዎች መካከል ተወዳድሮ በአንድ ቡድኑ ሶስተኛ ደረጃን አግኝቷል። ይህ ቡድን ሶስት ተማሪዎችን ይዞ በ8ኛው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ የፍጻሜ ውድድር አገሩን ወክሎ ለመሳተፍ ቻይና ገብቷል። ውድድሩ ከግንቦት 14 እስከ 18 ቀን 2016 ዓ.ም በቻይና ሼንዘን ከተማ ይካሄዳል።
ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ከግንቦት 16 እስከ 20/ 2015 ዓ.ም በቻይና ሼንዘን ከተማ በተካሄደው 7ኛው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ፍጻሜ ውድድር 9 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው ማጠናቀቃቸው ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስቴር ለውድድሩ ተሳታፊ ተማሪዎቹ መልካም ውጤትን ይመኛል።
Recent News
የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና
Jul 23, 2024
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር ውይይት አደረጉ
Jul 18, 2024
ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈታናን አስጀመሩ
Jul 10, 2024
አንጋፋው፣ ስመጥሩና ራስ ገዝ የሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስመረቀ
Jul 08, 2024
በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዙሪያ ከጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ
Jun 25, 2024
2ኛው አመታዊ አገር አቀፍ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ጉባኤ ተካሄደ
Jun 27, 2024