News Detail
May 09, 2024
635 views
የጃፓኑ ቶፓን ግራቪቲ የሕትመት ፋብሪካ በኢትዮጵያ የማምረት ሥራ ሊጀምር ነው ።
የጃፓኑ የሕትመት ፋብሪካ ቶፓን ግራቪቲ በኢትዮጵያ የማምረት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተገልጿል፡፡
ኩባንያው በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለሚገነባው ፋብሪካ የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋን ጨምሮ በርካታ ሚኒስትሮች ተገኝተዋል።
ቶፓን ግራቪቲ የህትመት ፋብሪካ በኢትዮጵያ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ የመማሪያ መጽሐፍትን በማተም በትምህርት ዘርፉ ላይ እያጋጠመ ያለውን የመጽሐፍ እጥረት ለመቅረፍ ይሰራልም ተብሏል።
ከዚህም በተጨማሪ ፋብሪካው ዓለም አቀፍ የደህንነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ ሚስጢራዊ ሕትመቶችን ለማተም እንደሚያስችልም ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከዚህ ቀደም በጃፓን፣ ቶኪዮ በሚገኘው ‘Toppan Gravity ‘ዋና መስሪያ ቤት የስራ ጉብኝት በማድረግ ከተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ እና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች ጋር የህትመት ሥራን በኢትዮጵያ መጀመር በሚቻልበት ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ይታወቃል።
Recent News
የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠና
Jul 23, 2024
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር ውይይት አደረጉ
Jul 18, 2024
ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈታናን አስጀመሩ
Jul 10, 2024
አንጋፋው፣ ስመጥሩና ራስ ገዝ የሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስመረቀ
Jul 08, 2024
በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዙሪያ ከጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ
Jun 25, 2024
2ኛው አመታዊ አገር አቀፍ የፍልሰት ጥናትና ምርምር ጉባኤ ተካሄደ
Jun 27, 2024