News Detail
May 09, 2024
853 views
የጃፓኑ ቶፓን ግራቪቲ የሕትመት ፋብሪካ በኢትዮጵያ የማምረት ሥራ ሊጀምር ነው ።
የጃፓኑ የሕትመት ፋብሪካ ቶፓን ግራቪቲ በኢትዮጵያ የማምረት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተገልጿል፡፡
ኩባንያው በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለሚገነባው ፋብሪካ የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋን ጨምሮ በርካታ ሚኒስትሮች ተገኝተዋል።
ቶፓን ግራቪቲ የህትመት ፋብሪካ በኢትዮጵያ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ የመማሪያ መጽሐፍትን በማተም በትምህርት ዘርፉ ላይ እያጋጠመ ያለውን የመጽሐፍ እጥረት ለመቅረፍ ይሰራልም ተብሏል።
ከዚህም በተጨማሪ ፋብሪካው ዓለም አቀፍ የደህንነት መስፈርቶችን የሚያሟሉ ሚስጢራዊ ሕትመቶችን ለማተም እንደሚያስችልም ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከዚህ ቀደም በጃፓን፣ ቶኪዮ በሚገኘው ‘Toppan Gravity ‘ዋና መስሪያ ቤት የስራ ጉብኝት በማድረግ ከተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ እና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች ጋር የህትመት ሥራን በኢትዮጵያ መጀመር በሚቻልበት ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ይታወቃል።
Recent News
Oct 16, 2024
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ
Sep 19, 2024
የትምህርት ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ
Oct 06, 2024
Oct 08, 2024
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል።
Oct 08, 2024
የሬሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
Oct 08, 2024
Sep 10, 2024
Sep 17, 2024