News Detail
Oct 17, 2025
826 views
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ከአለም የምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ዋና ምክትል ኃላፊ ጋር ተወያዩ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታዋ የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ምክትል ኃላፊ ሙቲንታ ሀምባይን (ዶ/ር) በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሁለቱ አካላት በቀጣይ የኢትዮጵያ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብርን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።
በዚሁ ጊዜ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የኢትዮጵያ መንግሥት ለትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለመርሃ-ግብሩ የሚመድቡት በጀት አየጨመረ መምጣቱንና ህብረተሰቡም ለመርሃ-ግብሩ ውጤታማነት የሚያደርገው ተሳትፎ በየጊዜው እያደገ የመጣ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የአለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ሙቲንታ በበኩላቸው የኢትዮጵያ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር በአፍሪካ ትልቁና ቀዳሚ መሆኑን ጠቅሰው በቅርቡ በተካሄደው አለም አቀፍ የትምህርት ቤት ምገባ ጥምረት ስብሰባ ላይ እውቅና የተሰጠውና በአርዓያነት የሚጠቀስ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት ለትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር መተግበር ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየተሰሩ ባሉ ሥራዎች ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡
Recent News
የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ።
Feb 27, 2026
አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርስቲ አመራሮች ኃላፊነታቸውን በትክክል እንዲወጡ ተጠየቀ ።
Feb 13, 2026