News Detail
Nov 22, 2024
1.4K views
የአውሮፓ ህብረት ERASMUS+ የትምህርትና ስልጠና ደጋፍና ትብብር አሰጣጥን አስመልክቶ ውይይት ተደረገ፡፡
የመረጃ ልውውጡ የአውሮፓ ህብረት በትምህርትና ስልጠና የሚሰጣቸውን ድጋፎች አሟጦ ለመጠቀም እንዲቻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የከፍኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ባስተላለፉት መልዕክት የአውሮፓ ህብረት በ “ERASMUS+” የትምህርትና ስልጠና ድጋፍና ትብብር እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
መስል ድጋፎችና ትብብሮች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አቅም ከመገንባትና አለም አቀፍ ትብብርን ከማሳደግ አኳያ ሚናቸው ከፍተኛ በመሆኑ የሚገኙ እድሎችን አሟጦ መጠቀም እንደሚገባ ሚንስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
የአውሮፓ ህብረት በኢትጵያ አምባሳደር ሆነው የተሰየሙት ክብርት ሶፊ ፍሮም ኤምስበርገር በበኩላቸው የአውሮፓ ህብረት ከዚህ ቀደም ለ650 ያህል ኢትዮጵያውን የነጻ ትምህርት እድል የሰጠ መሆኑን በመጥቀስ ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል ገልጸዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኤባ ሚጀና በበኩላቸው መሰል ድጋፎችና ትብብሮች የከፍተኛ ትምህርት ዘርፉን አቅም በመገንባት ረገድ በሚኖራቸው ፋይዳ ላይ ሠፊ ገለጻ አድርገዋል።
መርሃ ግብሩን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በበይነ መረብ ጭምር ታድመውታል፡፡
Recent News
የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ አዲስ ከተመደቡት የጣሊያን አምባሳደር ጋር ተወያዩ
Dec 25, 2025
የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተደረገላቸው አቀባበል
Dec 20, 2025
Dec 15, 2025