News Detail
Oct 06, 2024
63 views
የትምህርት ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በኢትዮጵያ የአለም ባንክ ዳይሬክተር ሜሪያም ሳሊም ጋር በመሆን በአዲስ አበባ ሁለት ት/ቤቶች ውስጥ ጉብኝት አካሂደዋል፡፡
የስራ ሀላፊዎቹ በወንድይራድና አፄ ናኦድ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤቶች ባካሄዱት ጉብኝት የመማር ማስተማር ስራው የሚከናወንባቸውን ስፍራዎች ጎብኝተዋል፡፡
ጉብኝቱን ተከትሎ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከመምህራንና የትምህርት አስተዳደር ባለሙያዎች ጋር ባደረጉት ውይይት መምህራኑ እና የትምህርት አስተዳደር ባለሙያዎች በጋራ በመሆን የተማሪዎችን ብቃት ለማሻሻልና የትምህርት ቤቶቹን የውስጥ አቅም ለማሳደግ እያደረጉት ላለው አስተዋጾ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ክብርት ወ/ሮ አየለች አክለው እንደገለጹት በመከናወን ላይ ያሉ ጅምር ስራዎች የተማሪዎችን ውጤት በማሻሻልና የትምህርት ቤቶቹን የውስጥ አቅም በመገንባት ረገድ በአጠቃላይ ለትምህርት ማህበረሰቡም ይሁን ለዘርፉ ተዋንያኖች መነሳሳትን የሚፈጥር በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአለም ባንክ ዳይሬክተር ሜሪያም ሳሊም በበኩላቸው መምህራኑ እና የትምህርት አመራሩ ላይ አሁን የሚታየው ቁርጠኝነትና ተነሳሺነት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችል መሆኑን በመግለጽ ለዚህም የአለም ባንክ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
Recent News
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ
Sep 19, 2024
የትምህርት ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ
Oct 06, 2024
Oct 08, 2024
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል።
Oct 08, 2024
የሬሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
Oct 08, 2024
Sep 10, 2024
Sep 17, 2024