News Detail

National News
Sep 19, 2024 58 views

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የኢንኩቬንሽን ማዕከላትን በማጠናከር ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል።
ስልጠናውን ያስጀመሩት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የኢንኩቬንሽን ማዕከላትን ማጠናከር በተቋማቱ ያለውን የተዛባ ሚዛን ያስተካክላል ብለዋል። አሁን ባለው ግምገማ በተቋሞቻችን ያለው የኢንኩቬንሽን ማዕከላት አሰራር ከዘመኑ ጋር ያልተራመደ በመሆኑ ስልጠና ማዘጋጀት ማሰፈለጉን ጠቁመው በቀጣይ በዚህ ዘርፍ ላይ ስራዎች በትኩረት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ሃላፊ አቶ ተሾመ ዳንኤል በበኩላቸው ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዩንቨርሲት ኢንዱስትሪ ትስስር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ኢንኩቬሽን ማዕከላት ኃላፊዎች የሚሰጠው ስልጠና ለዘርፉ የተሰጠውን ትኩረት እንደሚያሳይ ጠቁመው ሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይህንን የሪፎርም ተልዕኮ በብቃት መወጣት እንደሚገባ አሳስበዋል። አቶ ተሾመ አያይዘውም ስልጠናው በፈጠራ ስነምህዳር፣ በስራ ፈጠራ ማበልጸጊያ ማዕከላት እና የምርምር ውጤቶችን እና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ገበያ ለማስገባት በሚከናወኑ አስተዳደራዊ ስራዎች ላይ የሚስተዋለውን የግንዛቤ እጥረት መፍታትን ትኩረት ያደርገ መሆኑን ገልጸው ስልጠናውን በዘርፉ ልምድ ያካበቱ የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ባለሙያች እውቀታቸውን ይጋሩበት መሆኑን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ከየተቋማቱ የመጡ የስራ ሃላፊዎች ማዕከላቱ በሚጠናከሩበት ዙሪያ ውይይት ያደረጉ ሲሆን በስልጠናው ብዙ ልምድ እንዳገኙ ጠቁመዋል።
Recent News
Follow Us