News Detail
Aug 02, 2024
1.4K views
ስርዓተ ትምህርቱ የአገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታና ቀጣይ ጊዜያትን መሠረት ያደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አድርገዋል
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ሥርዓተ ትምህርቱ የአገሪቱን የአሁንና የመጪውን ጊዜ ፍላጎት ዝንዲሁም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማዕከል የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።
የአንድ አገር ስርዓተ ትምህርት የአገርን የረጅም ጊዜ ጥቅም ማስጠበቅ የሚችሉ ዜጎች ማፍራት መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ሲቪል ሰርቫንቱም ከማንኛውም የፓለቲካ ፓርቲ ተጽእኖ ነጻ ሆኖ በችሎታውና በብቃቱ ብቻ ህዝብና አገረ መንግስትን ማገልገል እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል።
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ሠራተኞችም የአገርና የህዝብን ጥቅም በማስጠበቅ ለተጀመሩ የለውጥና ዓበይት ስራዎች ውጤታማነት ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በውይይቱ ወቅት የአጠቃላይ ትምህርት፣ የከፍተኛ ትምህርት፣ የኢትዮጵያ ትምህርት ባለስልጣንና የአገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዕቅድ ከፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና የየተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
Recent News
የ 2017 ዓ. ም የዪኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ።
Oct 24, 2024
Oct 16, 2024
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ
Sep 19, 2024
የትምህርት ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ
Oct 06, 2024
Oct 08, 2024
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል።
Oct 08, 2024
የሬሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
Oct 08, 2024
Sep 10, 2024
Sep 17, 2024