News Detail

National News
Sep 17, 2024 375 views

ማስታወቂያ

ረቂቅ መመሪያን በውይይት ለማዳበር አስተያየት እንዲሰጥ ስለመጠየቅ
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ዘርፍ ሁለንተናዊ እድገት እና ጥራትን ለማረጋገጥ ትክክለኛ እና ጥራት ያለዉ የትምህርት መረጃ የማይተካ ሚና ሰላለዉ በዘርፉ የትምህርት መረጃ አሰተዳደር ስርዓት ግልፅነት እና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሰራር ለመፍጠር የሚያስችል የትምህርት መረጃ አሰተዳደር ስርዓት ረቂቅ መመሪያ አዘጋጅቷል።
የተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ፀድቆ ስራ ላይ ከመዋሉ በፊት በቀጥታ ህብረተሰቡ በሚሳተፍበት መድረክ አስተያየት እና ግብአት እንዲሰበሰብ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በመሆኑም መሰከረም 08/2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው የመስሪያቤታችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመገኘት ይፋዊ የህዝብ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ሰነዱን ለማዳበር የሚያስችል ግብአት ይሰጡን ዘንድ በአክብሮት እንጋብዛለን።
Recent News
Follow Us