News Detail
Sep 17, 2024
3K views
ማስታወቂያ
ረቂቅ መመሪያን በውይይት ለማዳበር አስተያየት እንዲሰጥ ስለመጠየቅ
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ዘርፍ ሁለንተናዊ እድገት እና ጥራትን ለማረጋገጥ ትክክለኛ እና ጥራት ያለዉ የትምህርት መረጃ የማይተካ ሚና ሰላለዉ በዘርፉ የትምህርት መረጃ አሰተዳደር ስርዓት ግልፅነት እና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሰራር ለመፍጠር የሚያስችል የትምህርት መረጃ አሰተዳደር ስርዓት ረቂቅ መመሪያ አዘጋጅቷል።
የተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ፀድቆ ስራ ላይ ከመዋሉ በፊት በቀጥታ ህብረተሰቡ በሚሳተፍበት መድረክ አስተያየት እና ግብአት እንዲሰበሰብ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በመሆኑም መሰከረም 08/2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው የመስሪያቤታችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመገኘት ይፋዊ የህዝብ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ሰነዱን ለማዳበር የሚያስችል ግብአት ይሰጡን ዘንድ በአክብሮት እንጋብዛለን።
Recent News
Sep 02, 2025
Aug 29, 2025
Aug 28, 2025
Aug 23, 2025