News Detail
Jul 18, 2024
651 views
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር ውይይት አደረጉ
የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ጋር በትምህርት ዘርፉ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በውይይታቸውም ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል። በኢትዮጵያ የኳታር አምባሳደር ከሀገራቸው የትምህርት ሚኒስቴር፣ ትምህርትን ከሚደግፉ የልማት ድርጅቶች ጋር በመተባበር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የኢትዮጵያን የትምህርት ሪፎርም ለመደገፍ በተለይም በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የት/ቤቶችን መስፋፋትና እድሳት፣ የት/ቤት ምገባ ለማገዝና እና የተለያዩ የመምህራን ክህሎት ማሻሻያ ስልጠናዎች ለመስጠት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት በዩኒቨርስቲዎች መካከል በሚደረግ ትብብር፣ በነጻ ትምህርት እድል፣ በጋራ የምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
Recent News
የ 2017 ዓ. ም የዪኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ።
Oct 24, 2024
Oct 16, 2024
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ
Sep 19, 2024
የትምህርት ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ
Oct 06, 2024
Oct 08, 2024
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል።
Oct 08, 2024
የሬሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
Oct 08, 2024
Sep 10, 2024
Sep 17, 2024