News Detail
Jul 10, 2024
1.2K views
ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈታናን አስጀመሩ
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በአብርሆት ቤተ-መጽሃፍት በመገኘት የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ብሄራዊ ፈተናን አስጀምረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በዚህ ዓመት እየተተገበረ ያለው የወረቀትና የኦን ላይን ፈተና (hybrid exam) መሆኑን አመልክተዋል። ለወደፊቱ ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን መፈተን ሲቻል የበለጠ ፈተናውን ከስርቆትና ከመኮራረጅ ከመታደጉም በላይ ለትምህርት ጥራት የበኩሉን ድርሻ ያበረክታል ብለዋል።
በተጨማሪም ፈተናውን ለማስተዳደር፣ ለቁጥጥር፣ ለህትመት፣ ለማጓጓዝ፣ ለሴኩዩሪቲ እና መሰል ወጭዎችን ለመቀነስ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በመጨረሻም የፈተናውን ድባብ ለማበላሸት ሀሰተኛ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ስለሚንሸራሸሩ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ አሳስበው ተማሪዎችም ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲሰሩ መክረዋል።
Recent News
Oct 16, 2024
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ
Sep 19, 2024
የትምህርት ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ
Oct 06, 2024
Oct 08, 2024
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል።
Oct 08, 2024
የሬሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
Oct 08, 2024
Sep 10, 2024
Sep 17, 2024