News Detail

National News
Oct 09, 2020 628 views

ባለሃብቶችና ድርጅቶች የትምህርት ዘርፉን በመደገፍ ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ የትምህርት ሚኒስቴር ጠየቀ።

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች የትምህርት ቤቶችን ዝግጁነት በተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውረው እየተመለከቱ ነው።

በአዲስ አበባ አካባቢዎች የሚገኙትን ትምህርት ቤቶችን ተዘዋውረው የተመለከቱት የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ፒ ኤች ዲ) ባለሃብቶችና ድርጅቶች የትምህርት ዘርፉን እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ኩባንያ በሰበታ ከተማ ያስገነባውን ዲማ ማኛ ትምህርት ቤት በመረቁበት ወቅት በሀገር ውስጥ የተሰማሩ ድርጅቶች በትምህርት ቤት ግንባታና በውሃ አቅርቦት እገዛ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ሚኒስትሩ በህዝቡ አስተዋፅኦ፣ በባለሃብቶች እንዲሁም በመንግስት ድጋፍ ከ 50ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን ገልፀዋል።

Recent News
Follow Us