News Detail

የሀገር ውስጥ ዜና
Oct 23, 2020 531 views

ኢትዮጵያ እና ሩስያ በትምህርት ዘርፍ የሚያደርጉትን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ፒ ኤች ዲ) የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌት ተረኪን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው የጋራ ኮሚሽን ጉዳይ እና በዚህ ዓመት በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የሁለቱ ሀገራት የጋራ ኮሚሽን በሚካሄድበት ሁኔታና ስለሚከናወኑ ተግባራት ምክክር አድርገዋል፡፡

በተጨማሪም በሩስያ መንግስት በሚሰጡ የነፃ ትምህርት እድሎች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡

በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢቭጌት ተረኪን ሩስያ ለትምህርት ዘርፉ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥልም ተናግረዋል፡፡

Recent News
Follow Us