News Detail
Oct 26, 2022
3.1K views
ከጥረት ውጭ የሚገኝ ውጤትን የሚጠየፍ ህዝብ እንዳለን ከፈተናው ሂደት ተገንዝበናል - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ12ኛ ክፍል መጠናቀቁን ተከትሎ በሰጡት መግለጫ፥ በፈተናው አሰጣጥ ሂደት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልዕኮን ማሳካት እንደሚችሉ አይተናል ብለዋል።
ከጥረት ውጭ የሚገኝ ውጤትን የሚጠየፍ ህዝብ እንዳለን ከፈተናው ሂደት ተገንዝበናል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ሂደቱ በህብረተሰቡ እገዛና ትብብር በዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻልም ያመላከተ እንደነበር ተናግረዋል።