News Detail
Jun 27, 2024
3.8K views
የ2016ዓ.ም የፋርማሲ የመዉጫ ፈተና (Exit Exam) ለተፈተናችሁ ተማሪዎች በሙሉ
ከሰኔ 14 እስከ 19 ቀን 2016 ዓ. ም በ 244 ፕሮግራሞች በ57 የመንግስትና በ124 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለነበሩ ተማሪዎች የመዉጫ ፈተና ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ለስድስት ቀናት የተሰጠው ፈተና ያለምንም እንከን የተጠናቀቀ ሲሆን ነገር ግን በመጨረሻው ቀን የተሰጠዉ የፋርማሲ ፈተና ብቻ የቴክኒክ ችግር አጋጥሞታል። ስለሆነው ትምህርት ሚኒስቴር ተማሪዎቹ ፈተናውን በድጋሜ እንዲወስዱ አመቻችቷል።
በዚሁ መሰረት ፈተናው በድጋሜ ቅዳሜ ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት ከ 3:00 ሰአት ጀምሮ እና ከሰአት ከ 8:00 ሰአት ጀምሮ ስለሚሰጥ ለፈተናው ተቀምጣችሁ የነበራችሁ የፋርማሲ ተማሪዎች በተፈተናችሁበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ በመገኘት በድጋሜ የሚሰጠውን ፈተና እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡
Recent News
Oct 16, 2024
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ
Sep 19, 2024
የትምህርት ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ
Oct 06, 2024
Oct 08, 2024
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል።
Oct 08, 2024
የሬሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
Oct 08, 2024
Sep 10, 2024
Sep 17, 2024