እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

ማስታወቂያ

ለፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራን አወዳድረን ለመቅጠር የምዝገባ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል።
ነገር ግን የዘንድሮ የክረምት ልዩ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች አቅም ግንባታ ስልጠና የተጠናቀቀው በቅርቡ በመሆኑ ምዝገባውን ማራዘም አስፈልጓል። በመሆኑም ምዝገባው እስከ ጳጉሜን 05/2017 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ መሆኑንን እየገለጽን ለማመልከት ፍላጎቱ ያላችሁ መምህራን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እድትመዘገቡ በድጋሚ እንገልጻለን ። ለመመዝገብ https://sbs.moe.gov.et/career/teacher ይጠቀሙ
ለፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራን አወዳድረን ለመቅጠር የምዝገባ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል።
ነገር ግን የዘንድሮ የክረምት ልዩ የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች አቅም ግንባታ ስልጠና የተጠናቀቀው በቅርቡ በመሆኑ ምዝገባውን ማራዘም አስፈልጓል። በመሆኑም ምዝገባው እስከ ጳጉሜን 05/2017 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ መሆኑንን እየገለጽን ለማመልከት ፍላጎቱ ያላችሁ መምህራን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እድትመዘገቡ በድጋሚ እንገልጻለን ። ለመመዝገብ https://sbs.moe.gov.et/career/teacher ይጠቀሙ
Sep 02, 2025 2.3K
የሀገር ውስጥ ዜና

የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደገበያ የማስገባት ተግባር የሪፎርም አካል ተደርጎ በትኩረት እየተሰራበት መሆኑ ተገለጸ።

ለዩኒቨርሲቲ እንዱስትሪ ትስስር ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተሮችና የኢንኩቤሽን ማዕከላት አስተባባሪዎች ስልጠና ተሰጥቷል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ፣ የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሃንዲሶ (ዶ/ር) በስልጠናው ላይ እንደገለጹት የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደገበያ የማስገባት ሥራ በአገር አቀፍ ደረጃ እንደዋና ዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት ይገኛል።
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተቋቋሙ 27 የኢንኩቤሽን ማዕከላትን የማጠናከርና ያላቋቋሙትም እንዲያቋቁሙ እየተደረገ መሆኑንም ዶ/ር ሠራዊት ተናግረዋል።
የኢንኩቤሽን ማዕከላት ማቋቋም የሥራ አጥነትን ችግር በማቃለል፣ የተግባር ልምምድ ለማድረግ በተለይም ክህሎትና ሥራ ፈጠራ ችግሮች ለመቅረፍ እንደሚያስችልም መሪ ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
የኢንኩቤሽን ማዕከላትን ማስፋፋት በተለያዩ የትምህርት መስኮች መካከል ሊኖር የሚችለውን መስተጋብርና ቅንጅት የተሻለ በማድረግ ፈጠራና የሳይንስ ዕውቀት እንዲዳብር ለማድረግ እንደሚያግዝም ዶ/ር ሠራዊት ጨምረው አስረድተዋል።
የተቋማት ትስስር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ አቶ ተሾመ ዳንኤል በበኩለቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ ራስ ገዝነት በሚያመሩበት ወቅት በፋይናንስ ራስን የመቻል ሂደትን የሚደግፉ ተግባራትን ማከናወን ቅድምያ የሚሰጠው አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህ እውን እንዲሆን የአዕምሯዊ ንብረትን፣ ቴክኖሎጂን እና የምርምር ውጤቶችን ወደ ገበያ በማስገብት ፤ የኢንኩቤሽን ማዕከላት ጥምረት መፍጠር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡
የሚሸጋገሩ የፈጠራ እና የቴክኖሎፐጂ ውጤቶች ተጽኖ መገምገም በሚያስችል ዲጂታል ፕላትፎረም የተደገፈ ስርዓት መዘርጋትና በፈጠራ ሀሳብ ላይ መዋለንዋያቸውን ማፍሰስ ለሚፈልጉ ኢንዱስትሪዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርላቸው አቶ ተሾመ አስገንዝበዋል፡፡
በትስስር አዋጅ 1298/2015 ማስፈጸሚያ መመሪያዎች፣ የምርምር እና ተክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ ገበያ የመስገባት ሂደት እና የቢዝነስን፣ ፈጠራ እና የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ማዕከላት አስተዳደር ዙሪያ ባተኮረው ስልጠና የዩኒቨርሲቲ እንዱስትሪ ትስስር ፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተሮችና የኢንኩቤሽን ማዕከላት አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል።
ለዩኒቨርሲቲ እንዱስትሪ ትስስር ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተሮችና የኢንኩቤሽን ማዕከላት አስተባባሪዎች ስልጠና ተሰጥቷል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ፣ የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሃንዲሶ (ዶ/ር) በስልጠናው ላይ እንደገለጹት የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደገበያ የማስገባት ሥራ በአገር አቀፍ ደረጃ እንደዋና ዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት ይገኛል።
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተቋቋሙ 27 የኢንኩቤሽን ማዕከላትን የማጠናከርና ያላቋቋሙትም እንዲያቋቁሙ እየተደረገ መሆኑንም ዶ/ር ሠራዊት ተናግረዋል።
የኢንኩቤሽን ማዕከላት ማቋቋም የሥራ አጥነትን ችግር በማቃለል፣ የተግባር ልምምድ ለማድረግ በተለይም ክህሎትና ሥራ ፈጠራ ችግሮች ለመቅረፍ እንደሚያስችልም መሪ ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
የኢንኩቤሽን ማዕከላትን ማስፋፋት በተለያዩ የትምህርት መስኮች መካከል ሊኖር የሚችለውን መስተጋብርና ቅንጅት የተሻለ በማድረግ ፈጠራና የሳይንስ ዕውቀት እንዲዳብር ለማድረግ እንደሚያግዝም ዶ/ር ሠራዊት ጨምረው አስረድተዋል።
የተቋማት ትስስር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ አቶ ተሾመ ዳንኤል በበኩለቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ ራስ ገዝነት በሚያመሩበት ወቅት በፋይናንስ ራስን የመቻል ሂደትን የሚደግፉ ተግባራትን ማከናወን ቅድምያ የሚሰጠው አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህ እውን እንዲሆን የአዕምሯዊ ንብረትን፣ ቴክኖሎጂን እና የምርምር ውጤቶችን ወደ ገበያ በማስገብት ፤ የኢንኩቤሽን ማዕከላት ጥምረት መፍጠር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡
የሚሸጋገሩ የፈጠራ እና የቴክኖሎፐጂ ውጤቶች ተጽኖ መገምገም በሚያስችል ዲጂታል ፕላትፎረም የተደገፈ ስርዓት መዘርጋትና በፈጠራ ሀሳብ ላይ መዋለንዋያቸውን ማፍሰስ ለሚፈልጉ ኢንዱስትሪዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርላቸው አቶ ተሾመ አስገንዝበዋል፡፡
በትስስር አዋጅ 1298/2015 ማስፈጸሚያ መመሪያዎች፣ የምርምር እና ተክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ ገበያ የመስገባት ሂደት እና የቢዝነስን፣ ፈጠራ እና የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ማዕከላት አስተዳደር ዙሪያ ባተኮረው ስልጠና የዩኒቨርሲቲ እንዱስትሪ ትስስር ፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተሮችና የኢንኩቤሽን ማዕከላት አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል።
Sep 02, 2025 842
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር የተመራ የልዑካን ቡድን ተቀብለው አነጋገሩ።

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ የእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ጊላድ ሻድሞን (Gilad Shadmon) የተመራ የልዑካን ቡድን አባላትን ተቀብለው በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርቱ ዘርፍ ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትር ዴኤታው በአገራቱ መካከል የከፍተኛ ትምህርት ትብብር በተለይም በአካዳሚክ ፣ በምርምር በዩኒቨርስቲ ኢንዱስትሪ ትስስር ከእስራኤል ዩኒቨርስቲዎች ልምድና ተሞክሮ መቅሰም እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
በፈጠራና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ፣ በግብርና ፣ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፣ በማዕድንና በሌሎችም ዘርፎች ትብብር ማሳደግ እንደሚያስፈልግም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።
የእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ጊላድ ሻድመን በበኩላቸው በኢትዮጵያና በእስራኤል መካከል የቆየ ወዳጅነትና ትብብር መኖሩን ጠቁመው አገራቸው በትምህርቱ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
እስራኤል በግብርና በአካባቢ ጥበቃ በተለይም በውሃና አፈር ጥበቃና አያያዝ፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በሌሎችም ያላትን ልምድ ማካፈል እንደምትችልም ገልጸዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ የእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ጊላድ ሻድሞን (Gilad Shadmon) የተመራ የልዑካን ቡድን አባላትን ተቀብለው በሁለቱ አገራት መካከል በትምህርቱ ዘርፍ ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ ሚኒስትር ዴኤታው በአገራቱ መካከል የከፍተኛ ትምህርት ትብብር በተለይም በአካዳሚክ ፣ በምርምር በዩኒቨርስቲ ኢንዱስትሪ ትስስር ከእስራኤል ዩኒቨርስቲዎች ልምድና ተሞክሮ መቅሰም እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
በፈጠራና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ፣ በግብርና ፣ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፣ በማዕድንና በሌሎችም ዘርፎች ትብብር ማሳደግ እንደሚያስፈልግም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።
የእስራኤል የክልል ትብብር ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር ጊላድ ሻድመን በበኩላቸው በኢትዮጵያና በእስራኤል መካከል የቆየ ወዳጅነትና ትብብር መኖሩን ጠቁመው አገራቸው በትምህርቱ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ ገልጸዋል።
እስራኤል በግብርና በአካባቢ ጥበቃ በተለይም በውሃና አፈር ጥበቃና አያያዝ፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በሌሎችም ያላትን ልምድ ማካፈል እንደምትችልም ገልጸዋል።
በውይይቱ ላይ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
Aug 29, 2025 507
የሀገር ውስጥ ዜና

የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና መምህራን የሚያስተምሩትን የትምህርት ዓይነት ይዘት በአግባቡ እንዲያውቁና እንዴት ማስተማር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረበት እንደነበር ተጠቆመ፤ ለሁለተኛ ደረጃ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ሲሰጥ የቆየው የክረምት ልዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተጠናቋል፡፡

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) እንደገለጹት ከሐምሌ 28/2017 እስከ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ለመምህራንና የት/ቤት አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መምህራን የሚያስተምሩትን የትምህርት ዓይነት ይዘት በአግባቡ እንዲያውቁና ለተማሪዎችም እንዴት ማስተማር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነበር ብለዋል፡፡
በስልጠናው መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮቹ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት ኖሯቸው ማስተማር እንዲችሉ ፣ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶችንም ተቋቁመው የመማር ማስተማር ስራን እንዴት መምራት እንዳለባቸው አቅም የገነቡበት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
ሰልጣኝ መምህራኑ የወሰዱት የማስተማር ስነ ዘዴ ስልጠናም ወቅታዊ ችግሮችን ለመፍታትም ሆነ እየተተገበረ የሚገኘውን ስርኣተ ትምህርት በአግባቡ መተግበርና መፈጸም እንደሚያስችላቸውም ዶ/ር ሙሉቀን አብራርተዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ አሰገደች መሬሳ በበኩላቸው ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ከ60 እስከ 120 ሰዓት በሶስት ተከፍሎ በተሰጠው የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና 64 ሺ 900 መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን ተካፋይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በስልጠናው ከ2 ሺ 400 በላይ የሚሆኑ አሰልጣኖችም መሳተፋቸውንና 184 ሺ የስልጠና ሞጁሎች ተዘጋጅተው መሰራጨታቸውን የዴስክ ኃላፊዋ ወ/ሮ አሰገደች ተናግረዋል፡፡
ሰልጣኞቹ የድህረ ስልጠና ምዘና ፈተና በበይነ መረብ መውሰዳቸውን ጠቁመው በቀጣይ ቀናት ውስጥ የይለፍ ቃል /Password/ እና የመጠቀሚያ ስማቸውን/Username/በመጠቀም ውጤታቸውን ማየትና ከ70 በመቶ ውጤት ያመጡ ሰልጣኞችም የምስክር ወረቀታቸውንም አውርደው መውሰድ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም ሃላፊዋ ለዚህ የመምህራንና የት/ቤት ስልጠና መሳካት አስተዋዕኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) እንደገለጹት ከሐምሌ 28/2017 እስከ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ለመምህራንና የት/ቤት አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መምህራን የሚያስተምሩትን የትምህርት ዓይነት ይዘት በአግባቡ እንዲያውቁና ለተማሪዎችም እንዴት ማስተማር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነበር ብለዋል፡፡
በስልጠናው መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮቹ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት ኖሯቸው ማስተማር እንዲችሉ ፣ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶችንም ተቋቁመው የመማር ማስተማር ስራን እንዴት መምራት እንዳለባቸው አቅም የገነቡበት እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
ሰልጣኝ መምህራኑ የወሰዱት የማስተማር ስነ ዘዴ ስልጠናም ወቅታዊ ችግሮችን ለመፍታትም ሆነ እየተተገበረ የሚገኘውን ስርኣተ ትምህርት በአግባቡ መተግበርና መፈጸም እንደሚያስችላቸውም ዶ/ር ሙሉቀን አብራርተዋል።
የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ አሰገደች መሬሳ በበኩላቸው ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም ከ60 እስከ 120 ሰዓት በሶስት ተከፍሎ በተሰጠው የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና 64 ሺ 900 መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን ተካፋይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በስልጠናው ከ2 ሺ 400 በላይ የሚሆኑ አሰልጣኖችም መሳተፋቸውንና 184 ሺ የስልጠና ሞጁሎች ተዘጋጅተው መሰራጨታቸውን የዴስክ ኃላፊዋ ወ/ሮ አሰገደች ተናግረዋል፡፡
ሰልጣኞቹ የድህረ ስልጠና ምዘና ፈተና በበይነ መረብ መውሰዳቸውን ጠቁመው በቀጣይ ቀናት ውስጥ የይለፍ ቃል /Password/ እና የመጠቀሚያ ስማቸውን/Username/በመጠቀም ውጤታቸውን ማየትና ከ70 በመቶ ውጤት ያመጡ ሰልጣኞችም የምስክር ወረቀታቸውንም አውርደው መውሰድ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም ሃላፊዋ ለዚህ የመምህራንና የት/ቤት ስልጠና መሳካት አስተዋዕኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
Aug 29, 2025 687
ማስታወቂያ

ማስታወቂያ

ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ተሰጥኦና ብቃት ያላቸው ተማሪዎች መልምሎ ልዩ ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ በፌደራል ደረጃ በተቋቋሙ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለማስተማር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት እነዚህን ትምህርት ቤቶች የሚመሩ ዳይሬክተሮችን ከመላ ሀገሪቱ አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ እና በልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ዳይሬክተር መሆን ለምትፈልጉ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመራሮች http://sbs.moe.gov.et/directors/apply ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ተሰጥኦና ብቃት ያላቸው ተማሪዎች መልምሎ ልዩ ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ በፌደራል ደረጃ በተቋቋሙ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለማስተማር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት እነዚህን ትምህርት ቤቶች የሚመሩ ዳይሬክተሮችን ከመላ ሀገሪቱ አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ እና በልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ዳይሬክተር መሆን ለምትፈልጉ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመራሮች http://sbs.moe.gov.et/directors/apply ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

Aug 29, 2025 984
የሀገር ውስጥ ዜና

ትምህርት ሚኒስቴር ከቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ልውውጥ ማዕከል ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሠነድ ተፈራረመ።

ትምህርት ሚኒስቴር ከቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ልውውጥ ማዕከል ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሠነድ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የተቋም ለተቋም ግንኙነትን በማጠናከር የሁለቱ ሀገራት የእውቀትና ክህሎት ሽግግርን ለማሳለጥ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ድኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ስምምነቱን በፈረሙበት ወቅት የቻይና መንግስት በኢትዬጵያ የትምህርት ልማት ዘርፍ ውስጥ ለሚያደርገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል
ሚኒስትር ድኤታው በማያያዝም ስምምነቱ ሀገራዊ ፍላጎት ላይ መሠረት በማድረግ በተለይም በማደግና በመስፋፋት ላይ ያሉ የዲጂታል፣ ሠው ሠራሽ አስተውሎ ፣ ሳይበር ሴኪዩሪቲና መሠል ትብብሮች ላይ የቻይና ባለሙያዎችንና ተቋማትን ድጋፍ እንደሚሹ አስገንዝበዋል።
መሠል ትብብሮች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማጠናከርና ቅርርቦሽን በመፍጠር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን አጋርነትና ትብብር በበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን ሚንስትር ድኤታው በማያያዝ ገልጸዋል።
የቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ማዕከል ሀላፊ ዩ ቻንግሺዩ በበኩላቸው ቻይና አሁን ለደረሠችበት የእድገት ደረጃ የአለም አቀፍ ትብብር ያለው ሚና ወሳኝ መሆኑን ትገነዘባለች ያሉ ሲሆን በትምህርትና ተያያዥ ልውውጦች ከኢትዮጵያ ጋር ተባብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ገልጸዋል።
እንደዚህ ዓይነት ትብብሮች መጪው ትውልድ በሀገራቱ መካከል ያለውን ትብብርና ጠንካራ ወዳጅነት አብዝቶ እንዲረዳ መሠረት የሚጥል በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው የማዕከል ሀላፊው አስገንዝበዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ልውውጥ ማዕከል ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ሠነድ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የተቋም ለተቋም ግንኙነትን በማጠናከር የሁለቱ ሀገራት የእውቀትና ክህሎት ሽግግርን ለማሳለጥ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ድኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ስምምነቱን በፈረሙበት ወቅት የቻይና መንግስት በኢትዬጵያ የትምህርት ልማት ዘርፍ ውስጥ ለሚያደርገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል
ሚኒስትር ድኤታው በማያያዝም ስምምነቱ ሀገራዊ ፍላጎት ላይ መሠረት በማድረግ በተለይም በማደግና በመስፋፋት ላይ ያሉ የዲጂታል፣ ሠው ሠራሽ አስተውሎ ፣ ሳይበር ሴኪዩሪቲና መሠል ትብብሮች ላይ የቻይና ባለሙያዎችንና ተቋማትን ድጋፍ እንደሚሹ አስገንዝበዋል።
መሠል ትብብሮች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በማጠናከርና ቅርርቦሽን በመፍጠር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን አጋርነትና ትብብር በበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን ሚንስትር ድኤታው በማያያዝ ገልጸዋል።
የቻይና ህዝባዊ ሪፐብሊክ ትምህርት ሚኒስቴር አለም አቀፍ የህዝብ ለህዝብ ማዕከል ሀላፊ ዩ ቻንግሺዩ በበኩላቸው ቻይና አሁን ለደረሠችበት የእድገት ደረጃ የአለም አቀፍ ትብብር ያለው ሚና ወሳኝ መሆኑን ትገነዘባለች ያሉ ሲሆን በትምህርትና ተያያዥ ልውውጦች ከኢትዮጵያ ጋር ተባብሮ ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ገልጸዋል።
እንደዚህ ዓይነት ትብብሮች መጪው ትውልድ በሀገራቱ መካከል ያለውን ትብብርና ጠንካራ ወዳጅነት አብዝቶ እንዲረዳ መሠረት የሚጥል በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው የማዕከል ሀላፊው አስገንዝበዋል።
Aug 29, 2025 452

ሚኒስትሮቻችን

MINISTER

ክቡር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

STATE MINISTER

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት

STATE MINISTER

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

STATE MINISTER

ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

የሚኒስትር አማካሪ ሚኒስቴር ዲኤታ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ