News Detail
Jul 18, 2024
911 views
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞችን አበረታቱ።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ በአብርሆት ቤተመጻህፍትና በመነን ትምህርት ቤት መፈተኛ ጣቢያዎች በመገኘት የፈተና እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል። ተፈታኝ ተማሪዎችንም አበረታተዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ከሐምሌ 03 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን በመፈተን ማስጀምሩ ይታወሳል። ይሄው አገር አቀፍ ፈተና ሁለተኛውን ዙር ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም በተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የቀጠለ ሲሆን በትግራይ ክልል በአሮጌው ካሪኩለም የሚፈተኑ ተማሪዎች በነገው እለት ሲያጠናቀቁ የሌሎች ክልሎች ተፈታኞች በዛሬው እለት የሚጨርሱ ይሆናል።
ክብርት ወ/ሮ አየለች ጉብኝቱን ባደረጉት ወቅት ለፈተናው የተደረገው ዘርፈብዙ ዝግጅትና ውጤት የተቋማት ትብብር የፈጠረው ውጤታማነት መሆኑን ገልጸዋል።
Recent News
የ 2017 ዓ. ም የዪኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ።
Oct 24, 2024
Oct 16, 2024
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ
Sep 19, 2024
የትምህርት ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ከፍተኛ ስራ ሃላፊዎች ትምህርት ቤቶችን ጎበኙ
Oct 06, 2024
Oct 08, 2024
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል።
Oct 08, 2024
የሬሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ
Oct 08, 2024
Sep 10, 2024
Sep 17, 2024