ትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ

የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ሙያ ፈቃድ አሰጣጥና እድሳት ዳይሬክቶሬት ዓለማ፣ተግባርና ኃላፊነት

1. ዓለማ

  • ጥራቱ የተጠበቀ ትምህርት በሀገሪቱ እንዲኖር ለማገዝ፣
  • በዕውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት የተሻለ አቅም ያላቸውንና በሥነምግባር የታነፁ ባለሙያዎችን  ወደ ሙያው ለመሳብና በሙያው ላይ እንዲቆዩ ለማስቻል፣
  • በሙያው ላይ ያሉ ነባር መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ብቃታቸውን እያሳደጉ ይበልጥ ተወዳዳሪ እየሆኑ ሙያውን ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ ለማድረግ፣

2. ተግባርና ኃላፈነት

  • የዳይሬክቶሬቱን ዕቅድ ማዘጋጀት፣ ማስተባበርና መምራት
    • የተቋሙን ስትራቴጂክ ዕቅድ መሠረት በማድረግ የዳይሬክቶሬቱን ስትራቴጂካዊና ዓመታዊ የሥራ እቅድና የበጀት ዕቅድ ማዘጋጀት፤ተግባራዊ ማድረግ፤
    • የሰው ሃይል፣ በጀት፤ ሎጂስትክስና ልዩ ልዩ ግብአቶች እንዲሟሉና ለታለመለት ዓላማ ማዋል፤
    • የስራ ክፍሉን የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቶችን ማዘጋጀት፣መገምገም፣ የአፈፃፀም ክፍተቶችን በመለየት ለሚመለከተው አካል ማቅረብ፤ የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳትን  በተመለከተ ከተገልጋዮች ለሚቀርቡ ቅሬታዎች ምላሽ ይሰጣል፣

2.2. ጥናቶችን ማካሄድ፣ ስትራቴጂዎችንና ፕሮጀክቶችን መቅረጽ፣

  • የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳትን ችግሮች የሚፈቱ ጥናትና ምርምር ለማካሄድ የሚረዳ የጥናት ዕቅድ (Research Proposal) ማዘጋት፤ ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ሙያዊ ሥነ-ምግባርን ተከትሎ ማሄድ፤
  • የጥናቱን ግኝት መሰረት በማድረግ የቀረቡ የማሻሻያና የመፍትሄ ምክረ ሃሳቦችን ስራ ላይ ማዋል፤
  • የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ስራዎችን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ፕሮጀክቶችን ይቀርጻል፤ የሀብት ማፈላለግ ሥራ ማከናወን፤

2.3. የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ማዕቀፎችን፣ደንብና መመሪዎችን ማዘጋጀት፤ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር አሰራር ሥርዓት መዘርጋት፤

  • የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮችንና ስልቶችን መዘርጋት፤
  • የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት አገልግሎትን በሚፈለገው ደረጃ ሥራ ላይ ለማዋል የሚያስችሉ የማስፈጸሚያ ማዕቀፎችን፣ ደንብና መመሪያዎችን ማዘጋጀትና ለሚመለከተው አካል አቅርቦ በማስጸደቅ መተግበር፤
  • የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ስርዓትን ሊያሻሽሉ የሚችሉ ምርጥ-ተሞክሮዎች የሚገኙባቸው አገሮችን እንዲሁም የአገር ውስጥ የስራ ክፍሎችን መለየት፣ ልምድ በመቅሰም  የተገኘውን የተሻለ ተሞክሮ ቀምሮ ከአገራዊና ከስራ ክፍሉ ተጫባጭ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ መተግበር፤
  • የሙያ ብቃት ምዘና ውጤትን መሠረት በማድረግ የክፍተት ዳሰሳ ጥናት በማካሄድ የሙያ ብቃት ምዘና አሰጣጥ  ሂደት ላይ ማሻሻያ ማድረግ፤
  • የተገልጋይ እርካታ ያለበት ደረጃ በዳሰሳ ጥናት በመፈተሽ ማሻሻል፤
  • ሌሎች የስራ ክፍሎች የሚያወጧቸው መመሪያዎች ከሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ማዕቀፎች፣ ደንብና መመሪያዎች ጋር መጣጣማቸውን ማረጋገጥ፤
  • የመቁረጫ ነጥብ ላስመዘገቡ ተመዛኞች የሙያ ፈቃድ የምስክር ወረቀት መስጠትና ማደስ፣

 2.4. የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠት፤ መምራትና ማስተባበር ፤  

  • በሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ዙሪያ በወጡ አዋጆች፣ማዕቀፎች፣ ደንብ፣ መመሪያዎች፣ ስታንዳርዶችና በምዘና መሳሪያዎች ዝግጅት ላይ ሥልጠናዎችን መስጠት፣
  • የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ግንዛቤ በተጠቃሚው ዘንድ እንዲሰርፅ የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ-ጥናት ያካሄዳል፤ አገር አቀፍ የምክክር መድረኮችን ያዘጋጃል፤

2.5. ለመምህራንና ለትምህርት ቤት አመራሮች ሙያ ብቃት የፅሁፍ ምዘናና የማህደረ ተግባር መመዘኛ ማሳሪዎችን ማዘጋጀትና ማስተዳደር

  • የምዘና ማዕቀፍ ማዘጋጀት፤
  • በተዘጋጀው የምዘና ማዕቀፍ መሰረት  የጽሁፍ እና የማህደረ ተግባር  ምዘና መሳሪያዎች እንዲጋጁ ማድረግ፣ የናሙና ምዘና (Pilot Test)ማካሄድና የምዘና ጥራቱን ማረጋገጥ፤
  • የፅሁፍ ምዘናውን በማካሄድ የመጀመሪያ ዙር እርማት ተካሂዶ ውጤቱ በየምዘና  ጣቢያው እንዲገለጽ ማድረግ፤
  • የማህደረ ተግባር (Portfolio) ምዘና የሚወስዱ ተመዛኞችን በመለየት ምዘና ማካሄድ፤
  • የሙያ ፈቃድ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት (Certificate) ማዘጋጀትና በክልሎች ጠያቂነት ለሚመለከታቸው እንዲደርሳቸው ማድረግ፤

2.6. በምዘና ውጤት የታዩ የተመዛኝ የይዘትና  የማስተማር ሥነ-ዘዴ የዕወቀትና የክህሎት ክፍተቶችን በመተንተንና (Gap Analysis) በመለየት ግኝቱን ለባለድርሻ አካላት ማቅረብ

  • የተመዛኞችን የየትምህርት ዓይነት እና የማስተማር ሥነ-ዘዴ እንዲሁም የአመራር ምዘና ክፍተቶችን (Gap Analysis) ትንተና ግኝት ከትምህርት ፖሊሲ አንጻር የተቃኘ (policy brief) ሰነድ አዘጋጅቶ ለሚመለከተው አካል ማቅረብ፤ 

2.7. የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት ሥራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ

  • በሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት አፈፃፀም ዙሪያ የክትትል፣ ድጋፍ፣ ግምገማ እና ግብረ-መልስ ሥራዎችን ማከናወን፤